Вы находитесь на странице: 1из 127

አማርኛ

የመምህር መጽሐፍ
4ኛ ክፍል

አዘጋጆች
ፀጋዬ በየነ አሸናፊ
ፋሲል መኳንንት ያለው

አርታኢዎች
ቻላቸው ገላው ሰጠኝ
አፀደ ማሩ ደሴ

ዲዛይነር
ገነት አባተ መኮንን

ቡድን መሪ
ማረው ዓለሙ ተሰማ (ፒኤች ዲ)

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ትምህርት ቢሮ


ይህ መጽሐፍ የተዘጋጀው በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በተመደበ በጀት በአብክመ ትምህርት
ቢሮና በምሁራን መማክርት ጉባዔ ትብብር ነው።

የመጽሐፉ ሕጋዊ የቅጂ ባለቤት © 2015 ዓ.ም. አብክመ ትምህርት ቢሮ ነው።

ምሁራን መማክርት ጉባዔ


ማውጫ

የመምህር መጽሐፍና የማስተማር መርሖች����������������������������������������������������������������������������������� iv

ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ���������������������������������������������������������������������������������������������������������� 1

ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት������������������������������������������������������������������������������������������������� 12

ምዕራፍ 3 መረዳዳት������������������������������������������������������������������������������������������������������������� 23

ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ������������������������������������������������������������������������������������������������������������ 33

ምዕራፍ 5 ጉብኝት���������������������������������������������������������������������������������������������������������������� 44

ምዕራፍ 6 ስፖርት����������������������������������������������������������������������������������������������������������������� 54

ምዕራፍ 7 ዉኃ�������������������������������������������������������������������������������������������������������������������� 65

ምዕራፍ 8 ድርድር���������������������������������������������������������������������������������������������������������������� 77

ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ����������������������������������������������������������������������������������������������������� 89

ምዕራፍ 10 ንግድ�������������������������������������������������������������������������������������������������������������� 100

ዋቢ መጻሕፍት�������������������������������������������������������������������������������������������������������������������� 111

iii
የመምህር መጽሐፍና የማስተማር መርሖች

መግቢያ

ይህ የመምህር መጽሐፍ በፍኖተካርታውና በአገርአቀፍ ምዘናዎች ምክረሐሳቦች መሠረት በ2013 ዓ.ም. በተደረገው
የሥርዓተትምህርት ለውጥ መነሻነት የተዘጋጀ ነው። በመሆኑም በመጽሐፉ ዝግጅት የሚከተሉት ጉዳዮች ልዩ ትኩረት
ተሰጥቷቸዋል፤
1. የተማሪዎችን በጥልቀት የማሰብ፣ የመተንተን፣ የመጠየቅ፣ ችግር የመፍታት፣ የመወሰን፣ የመግባባትና የመገምገም ክህሎት
የሚያሳድጉ ዓይነተብዙ ተግባራት ተካትተዋል፤
2. የተማሪዎችን አቀላጥፎ የማንበብ፣ የማዳመጥ፣ የመናገርና የመጻፍ ችሎታ የሚያጎለብቱ ታሪኮችና ተዛማጅ ተግባራት
እንዲኖሩ ተደርጓል፤
3. የትምህርቱ አቀራረብ ከይዘትተኮር ይልቅ ወደተግባርተኮር እንዲያመዝን ሆኗል፤
4. አገርበቀል እውቀቶች እንደአስፈላጊነታቸው በታሪኮች፣ በምንባቦችና በተግባራት ውስጥ ተካትተዋል፤
5. የባሕላዊ ማንነትንና የአርበኝነትን ፋይዳዎች የሚያስገነዝቡ ታሪኮች፣ ምንባቦች፣ ሥነግጥሞችና ሥዕሎች እንደአስፈላጊነታቸው
ተካትተዋል፤
6. ተማሪዎች በአብዛኛው በትብብር የሚማሩባቸው እድሎች ተመቻችተዋል፤
7. ለመማር የመማር ክህሎቶችን ለማጎልበት ሲባል፣ ተማሪዎች በየምዕራፎቹ አራቱን ክሂሎችና ሰዋስዋዊ ይዘቶች የሚማሩባቸው
ዓይነተብዙ ብልሀቶች ተካትተዋል፤
8. የተማሪዎችን የፈጠራ ችሎታ ለማጎልበት ሲባል ቋንቋውን ፈጥረው የሚጠቀሙባቸው በርካታ እድሎች ተመቻችተዋል፤
9. ሥርዐተፆታንና አካቶ ትምህርትን ከግምት ለማስገባት በታሪኮች፣ በምንባቦች፣ በሥዕሎችና በተዛማጅ ተግባራት እንዲሁም
በቋንቋው ትምህርት ይዘት አቀራረቦች ላይ ጥንቃቄ ተደርጓል።

የመምህር መጽሐፉ የሕጻናትን በአማርኛ ቋንቋ በትኩረት የማዳመጥ፣ የመናገር፣ በጥልቀት የማንበብና የመጻፍ ችሎታ ለማበልፀግ
በሚል ታሳቢ የተዘጋጀ ነው። የመጽሐፉ ዝግጅት በተጨማሪም ሕጻናት ማንበብና መጻፍ እንዴት እንደሚማሩ የተካሄዱ ምርምሮችን
ግኝቶችና የአማርኛ ቋንቋን መሠረታዊ ባህርያት መሠረት ያደረገ ነው። የትምህርት ይዘቶቹ በአሥር ምዕራፎች የተደራጁ ናቸው፤
የመጀመሪያዎቹ ዐምስት ምዕራፎች የትምህርት ይዘቶች በመጀመሪያው መንፈቀዓመት፣ ቀሪዎቹ ዐምስት ምዕራፎች ደግሞ
በኹለተኛው መንፈቀዓመት እንዲጠናቀቁ ሆነው የቀረቡ ናቸው። የአንድ ምዕራፍ የትምህርት ይዘቶች ደግሞ በሦስት ሳምንታት
እንዲጠናቀቁ ታስበው ነው የተደራጁት። የየምዕራፎቹ የትምህርት ይዘቶች በአንድ ነጥብ በተለዩ ሦስት ቁጥሮች የተወከሉ ናቸው፤
የመጀመሪያው ቁጥር ምዕራፍን፣ ኹለተኛው ቁጥር ሳምንትንና ሦስተኛው ቁጥር ቀንን የሚወክሉ ናቸው። ለምሳሌ፣ 1.1.1 የሚሉ
ቁጥሮች ምዕራፍ አንድን፣ ሳምንት አንድንና ቀን አንድን በቅደምተከተል ይወክላሉ፤ እንዲሁም 10.2.3 የሚሉ ቁጥሮች ምዕራፍ
አሥርን፣ ሳምንት ኹለትንና ቀን ሦስትን በቅደምተከተል ይወክላሉ።
በአጠቃላይ የመምህርና የተማሪ መጻሕፍቱ የተዘጋጁት ለ150 የትምህርት ቀናት ነው። ይህም በዓመቱ መጀመሪያ የተማሪዎች
ምዝገባንና የፈተና ቀናትን የሚጨምር አይደለም። ይሁንእንጂ በየትምህርትቤቱ የዓመቱ የትምህርት ቀናት በሥርዐተትምህርቱ
ከታሰበው በላይ ሊሆኑ ስለሚችሉ መምህራን የ150 ቀኑን ትምህርት ጨርሻለሁ፤ በማለት ሳይዘናጉ ተማሪዎች ያስቸገሯቸውን
የትምህርት ይዘቶች በዕለታዊ የትምህርት ዕቅድ እየታገዙ ማስተማርና ማለማመድ ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም ተማሪዎች
ለየክፍል ደረጃው የተዘጋጁትን አጋዥ የንባብ መጻሕፍት በክፍል ውስጥ በማንበብ እንዲለማመዱም ክፍለጊዜዎችን መጠቀም ተገቢ
ይሆናል።

iv
የመምህር መጽሐፉ በአብዛኛው የሕጻናቱን መማር ለማገዝ የተማሪ መጽሐፉን እንዴት መጠቀም እንደሚቻል ግልፅ መመሪያ
ያቀርባል። በተጨማሪም ተከታታይ ምዘናን እንዴት መተግበር እንደሚቻልና በትምህርቱ ሂደት ውስጥ የሥርዓተፆታንና አካትቶ
ትምህርትን እንዴት ማረጋገጥ አንደሚገባ ድጋፍ ይሰጣል።

የማንበብ/የመጻፍ አላባውያን
ሕጻናት ጠንካራ አንባቢና ጻፊ እንዲሆኑ ሊያዳብሯቸው የሚገቡ ዐምስት የማንበብ/የመጻፍ አላባውያን መኖራቸውን በመስኩ
የተደረጉ ምርምሮች ያመለክታሉ። ሕጻናቱ ራሳቸውን የቻሉ አንባቢዎች/ ፃፊዎች እንዲሆኑ ለመርዳት መምህራን ሥርዓት ባለውና
ግልጽ በሆነ መንገድ እነዚህን አላባውያን ማስተማር ይጠበቅባቸዋል። ሥርዓት ባለው ሁኔታ ሲባልም በትምህርቱ ሂደት አንዱም
ተፈላጊ አላባ ሳይዘለል ክሂሎችን ርስበርስ እንዲደጋገፉ አድርጎ ከቀላል ወደከባድ ማስተማር ማለት ነው። አምስቱ የማንበብ/ የመጻፍ
አላባውያን የሚባሉትም የሚከተሉት ናቸው፤
1. የንግግር ድምጾች ግንዛቤ
2. ትዕምርተድምጻዊ ግንዛቤ
3. አቀላጥፎ ማንበብ
4. የቃላት እውቀት
5. አንብቦ/አዳምጦ መረዳት
ቋንቋን በተመለከተ ሌሎች በጣም ጠቃሚ አላባውያን ቢኖሩም፣ እነዚህ ዐምስት አላባውያን ግን ለሕጻናት ቅድሚያ ሰጥተን
ልናስተምራቸው የሚገቡ ክሂሎች ናቸው። አላባውያኑን በአግባቡ ማስተማር ማለት ሕጻናቱ ራሳቸውን ችለው የሚያነቡና የሚጽፉ
እንዲሆኑ የሚያስችሏቸውን መሠረታዊ ክሂሎች ማስገንዘብ ማለት ነው።
የንግግር ድምጾች ግንዛቤ፡- የንግግር ድምጾችን የመስማት፣ የመለየትና የመገንዘብ ችሎታ ነው። ይህ አላባ በጣም ጠቃሚ ነው፤
ምክንያቱም፣
ƒƒ ድምጾችን ከፊደሎችጋር ለማዛመድ በጣም አስፈላጊ ስለሆነ ነው፤
ƒƒ ማንበብንና ፊደላትን በሥርዓት ሰድሮ ቃላትን ለመጻፍ ስለሚያግዝ ነው።
የንግግር ድምጾች ግንዛቤ ቃላትን፣ ቀለሞችን፣ ዓረፍተነገሮችን በቃል በሚደረግ ልምምድ ብቻ የሚዳብር ነው። በተጨማሪም
በመዝሙር መልክም በሚደረግ ልምምድ ሊጎለብት ይችላል። በዚህ መጽሐፍ የንግግር ድምፆች ግንዛቤ ትምህርት በአብዛኛው
የሚተኮርበት በአንደኛ ክፍል ነው።
ትዕምርተድምጻዊ ግንዛቤ፡- ፊደሎችን ከሚወክሏቸው ድምጾች ጋር አገናኝቶ የመረዳት ችሎታ ነው። ትእምርተድምጻዊ ግንዛቤ
በጣም አስፈላጊ ነው፤ ምክንያቱም፣
ƒƒ ቃላትን ለይቶ ለመጥራት ያስችላል። ይህም ሕጻናቱ ራሳቸውን የቻሉ አንባቢዎች እንዲሆኑ ያግዛቸዋል፤
ƒƒ የፊደላት አሰዳደር ሥርዓትን ግንዛቤ ያግዛል፤ በዚህም ተማሪዎች የሚያዳምጧቸውን ድምጾች ከትክክለኛዎቹ ፊደሎች ጋር
ማዛመድ ይችላሉ።
ትዕምርተድምጻዊ ግንዛቤ እያንዳንዱን ፊደልና የሚወክለውን ድምጽ በማስተማር ይዳብራል። በተጨማሪም የቃላቱን ፊደሎች፣
ቀለሞች ወይም አካላት (ክፋዮች) የማጣመርና የመነጠል መለማመጃዎችን በመስጠት ይጎለብታል።
አቀላጥፎ ማንበብ፡- አቀላጥፎ ማንበብ ጽሑፍን በትክክልና በተገቢው ፍጥነት ማንበብና የተነበበውን የማስታወስ ችሎታ ነው።
በተጨማሪም በተገቢው አገላለጽ (የድምጽ ቃናንና ጫናን ለይቶ) ማንበብን ያካትታል። አቀላጥፎ ማንበብ አስፈላጊ የሚሆንበት
ምክንያት ተማሪዎች ያለችግር ማንበብ ከቻሉ፣ በመረዳት ላይ ማተኮር ስለሚችሉ ነው።
ተማሪዎች 2ኛ ከፍልን ሲያጠናቅቁ በቃላት ደረጃ ከማንበብ በሐረግ ደረጃ በፍጥነት ወደማንበብ ችሎታ ይሸጋገራሉ።

v
የንግግርና የጽሑፍ አቀላጥፎ በተገቢ ሁኔታ ራስን መግለጽንም ይመለከታል። ይህ ደግሞ ቋንቋውን በትክክል መጠቀምንና ሐሳብን
ለሌላ አካል በንግግርም ሆነ በጽሑፍ በግልጽ ማስተላለፍን ይጨምራል።
አቀላጥፎ ማንበብ ሊዳብር የሚችለው በርካታ ልምምዶችን ከተገቢ ግብረመልሶች ጋር በመስጠት ነው። በመሆኑም የቃልና የጽሑፍ
አቀላጥፎ የሚዳብረው ተማሪዎች ራሳቸውን እንዲገልጹ በተቻለ መጠን በርካታ ዕድሎችን ከተገቢ ግብረመልሶች ጋር በመስጠት
ነው።
የቃላት እውቀት፡- ቃላትን የመለየት/የማወቅና ፍቻቸውን የመገንዘብ ችሎታ ነው። ምንምእንኳ ቃላትን ማንበብ ቢማሩም የተወሰኑ
ቃላትን ብቻ የሚያውቁ/የሚችሉ ተማሪዎች ትርጉምን ለመፍጠር/ ትርጉም ያለው ነገር ለማፍለቅ ይቸገራሉ። ስለሆነም ይህም አላባ
በጣም አስፈላጊ ነው። ምክንያቱም፣
ƒƒ ለተማሪዎች አቀላጥፎ ማንበብ አሰተዋጽዖ ያላቸውን ቃላት ከጽሑፍ ውስጥ ለይቶ የማውጣት ሂደትን ያቀላጥፋል፤
ƒƒ ተማሪዎች የሚያነቡትን እንዲረዱ ያስችላል፤
ƒƒ ተማሪዎች ሐሳባቸውን ግልጽ በሆነ መንገድ እንዲያስተላልፉ ያስችላል።
የቃላት ዕውቀት የሚዳብረው አዳዲስ ቃላትን ከነፍቻቸው በማስተማር፣ ተማሪዎች በንግግርም ሆነ በጽሑፍ ቃላትን
እንዲጠቀሙባቸው በማበረታታት፣ ከሚያነቡት ወይም ከሚያዳምጡት ጽሑፍ ውስጥ የቃላትን ፍቺ የሚያገኙበትን ብልሃት
(ስትራተጂ) እንዲማሩ በማድረግ ነው። የ2ኛ ክፍል ተማሪዎች ቃላትን በዓይነት ይመድባሉ፤ ለ2ኛ ክፍል ጠቃሚ የሆኑ የትምህርት
(የትምህርቤት) ቃላትን ይማራሉ፤ የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት ዓረፍተነገሮች ለመፃፍ ይጠቀሙባቸዋል።
አዳምጦ/አንብቦ መረዳት፡- አንድን ጽሑፍ ወይም ንግግር መረዳትና መተርጎም መቻል ነው። በተጨማሪም የማዳመጥና የማንበብ
የመጨረሻ ግብም ነው። ይህ ክሂል ቀጥተኛ መረዳትን ወይም በጽሑፍ ውስጥ ያለን መረጃ ማስታወስን፣ ፈልፍሎ መረዳትን
ወይም በቀጥታ ያልተገለጸን መረጃ መረዳትንና የመረዳት ስልቶችን ወይም ጽሑፉን ለመረዳት ወይም ለመተርጎም አንባቢዎች
የሚጠቀሙባቸውን ብልሃቶች (ስትራተጂዎች) ያጠቃልላል። ይህ ክሂል በጣም አስፈላጊ ነው፤ ምክንያቱም፣
ƒƒ ተማሪዎች በሁሉም ትምህርቶች በማንበብ እንዲማሩ ብቁ ያደርጋል፤
ƒƒ ተማሪዎች ራሳቸውን ችለው የሚያነቡና የሚያዳምጡ እንዲሆኑ ያስችላል፤ ከዚህም በላይ ተማሪዎች በሕይወት ዘመናቸው
ለመማርና ከተለያዩ ምንጮች መረጃ ለማግኘት ክሂሉን ይጠቀሙበታል።
አዳምጦ/ አንብቦ መረዳት የሚዳብረው በቅድመማዳመጥ/ማንበብ፣ በማዳመጥ/በማንበብ ሂደትና በድኅረማዳመጥ/ማንበብ
ተግባራት ነው። ተማሪዎች ስለጽሑፉ (በቅድመማዳመጥ/ንባብና በማዳመጥ/በማንበብ ሂደት ወቅት) እንዴት መገመት እንደሚችሉ፣
መረዳታቸውን (በራሳቸው) መቆጣጠር አንዲችሉና ያዳመጡትን ወይም ያነበቡትን እንዴት መገምገም እንደሚችሉ መማር
አለባቸው። ለምሳሌ፣ የ2ኛ ክፍል ተማሪዎች ይዘትተኮርና አመራማሪ ጥያቄዎችን ለመመለስ ልምምድ ያደርጋሉ። በሚያነቡበት
ወቅት የራሳቸውን ግንዛቤ ማረጋገጥ (መከታተል) የሚችሉበትን ሁኔታ ይማራሉ። በተጨማሪም ስለጽሑፉ ያላቸውን የግል ሐሳብ
እንዴት እንደሚገልፁ ይማራሉ።

የትምህርቱ ክፍሎች
ሁሉም የቋንቋ ክሂሎች (ማዳመጥ፣ መናገር፣ ማንበብና መጻፍ) ይዘቶች፣ የማንበብና የመጻፍ አላባውያንን በሚያዳብሩበት መልክ
ሆነው ተደራጅተዋል። ይህም ማለት፣
ƒƒ የምንባብ ይዘቶች (ጭብጦች)ና ንኡሳን ርዕሰጉዳዮች በጥቅም ላይ የዋሉት የማንበብንና የመጻፍን አላባውያንን ለማስተማር
ምንጭ በመሆን ነው፤ የቋንቋ ትምህርት ይዘቶችን ለማስተማር በአውድነት ከማገልገል ውጪ በራሳቸው ትምህርት
አይደሉም ማለት ነው፤
ƒƒ በሁሉም ዋና ዋና ምዕራፎች አራቱ የቋንቋ ክሂሎች ተዋህደው ቀርበዋል።

vi
የተማሪ መጽሐፍና የመምህር መጽሐፍ እያዳንዳቸው በሳምንታዊ ትምህርቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው። በተጨማሪም በተማሪ መጽሐፍና
በመምህር መጽሐፍ ውስጥ እያንዳንዱ ትምህርት በሥዕላዊ ምልክቶች የተጠቆሙ የትምህርት ክፍሎች አሉት። በእያንዳንዱ ምዕራፍ
ሥርም በተማሪዎች የሚሠሩ የተለያዩ ተግባራት አሉ። ብዙዎቹ ትምህርቶች ባብዛኛዎቹ ምዕራፎች ውስጥ ቢገኙም አንዳንድ
ትምህርቶች ግን የሚገኙት በተወሰኑ ምዕራፎች ብቻ ነው። ይሁንአንጂ ሁሉም የማንበብና የመጻፍ አላባውያንና ሁሉም የቋንቋ
ክሂሎች በእያንዳንዱ ሳምንት ትምህርት ውስጥ እንዲካተቱ ተደርጓል።

የትምህርቱ ክፍሎችም፤

የማዳመጥ ምንባብ
ይህ ክፍል በአዳምጦ መረዳት ላይ ያተኮረ ነው። ተግባራቱም የሚከተሉትን የያዙ ናቸው፤
ƒƒ ተማሪዎች በመምህር የሚነበብ ታሪክ ወይም መረጃሰጪ ጽሑፍ ያዳምጣሉ።
ƒƒ ካዳመጡት ምንባብ ውስጥ የወጡ ጥያቄዎችን ይመልሳሉ።
ƒƒ ስለታሪኩ ያላቸውን አስተያየት መግለፅ ይጀምራሉ።
ƒƒ ከታሪኩ አላባዎች ውስጥ፤ ባለታሪኮችን፣ የታሪኩን ጊዜና ስፍራ መለየት ይጀምራሉ።
ƒƒ በታሪኩ ውስጥ የሚገኙ አዳዲስ ቃላትን ይማራሉ።
ƒƒ በታሪኩ ላይ ይወያያሉ።
ƒƒ ስለታሪኩ በተወሰኑ ቃላት ይጽፋሉ፤ ወይም ሥዕል ይሥላሉ።

አዲስ ወይም ተተኳሪ ፊደል


ይህ ክፍል ለአንደኛ ክፍል ተማሪዎች፣ ባልተማሯቸው የመጨረሻ ፊደላት ላይ ያተኩራል። ተግባራቱም የሚከተሉትን ሊያካትት
ይችላል፡-
ƒƒ አዳዲስ ፊደላትን ይተዋወቃሉ፤
ƒƒ ፊደላቱ በቃላት ውስጥ ያላቸውን ንበት (ምን ዓይነት ድምጽ እንዳላቸው) ይማራሉ፤
ƒƒ በያንዳንዱ ፊደል የሚጀምሩ ወይም የሚጨርሱ ቃላትን ይለያሉ።

ማጣመር/መነጠል
ይህ ክፍል ልጆቹን ቃላት ለማንበብና በተገቢ የፊደል አሰዳደር ሥርዓት ለመጻፍ እንዲያግዝ ሆኖ ቃላትን በማንበብና ወደተለያዩ
ክፍሎች በመነጠል ወይም በማጣመር ላይ ያተሉራል። ተግባራቱም የሚከተሉትን ያካትታሉ።
ƒƒ ቃላትን “ማጣመር”፡- ቃላቱ የተመሠረቱባቸውን ፊደሎች ወይም የቃላቱን የተነጣጠሉ አሀዶች ለየብቻ ያነባሉ፤ መልሰውም
አንድ ላይ ይሏቸዋል፤
ƒƒ ቃላትን “መነጠል”፡- ቃላቱን ያነባሉ፤ ቀጥለውም ወደፊደላት ወይም ወደአነስተኛ አሀዶች ይነጣጥላሉ፤
ƒƒ ፍቺ ያላቸውን የቃላቱን አሀዶች (ምዕላዶችን) ለይተው ያነባሉ።

vii
ማንበብ
ይህ ክፍል ሕጻናቱ ቃላትን ለመጥራትና ተዘውታሪ ቃላትን ለመገንዘብ እንዲችሉ ዓረፍተነገሮችን፣ አጫጭር ታሪኮችን ወይም
መረጃሰጪ ምንባቦችን እንዲያነቡ በማድረግ ላይ ያተኩራል። በአንብቦ መረዳትም ላይ ያተኩራል። ተግባራቱም የሚከተሉትን
ያጠቃልላሉ፤
ƒƒ አንብቦ መረዳትን/ አቀላጥፎ ማንበብን፤
ƒƒ ከምንባቡ የወጡ ጥያቄዎችን መመለስን፤
ƒƒ ስለምንባቡ ያላቸውን የግል አስተያየት መግለጽን፤
ƒƒ ከታሪክ አላባዎች ባለታሪኮችን፣ የታሪኩን ጊዜና ስፍራ መለየት መጀመርን፤
ƒƒ በምንባቡ ላይ መወያየትን፤
ƒƒ ምንባቡን የሚመለከት ጽሑፍ መጻፍን።

የቃላት ዕውቀት
ይህ ክፍል አዳዲስ ቃላትን በመማርና በመጠቀም ላይ ያተኩራል። ተግባራቱም የሚከተሉትን ሊያካትቱ ይችላሉ፡-
ƒƒ አዳዲስ ተተኳሪ ቃላት መማርን፤
ƒƒ አዳዲስ ቃላትን ከሥዕሎች ወይም ከፍቻቸው ጋር ማዛመድን፤
ƒƒ ቃላትን መመደብን፤
ƒƒ ለቃላት ተመሳሳይና ተቃራኒ መስጠትን፤
ƒƒ ቃላቱን በዓረፍተነገር ውስጥ መጠቀምን፤
ƒƒ ለ2ኛ ክፍል ትምህርታቸው ጠቃሚ የሆኑ አዳዲስ ትምህርታዊ/የት/ቤት ቃላትን መማርን።

መጻፍ
ይህ ክፍል ፊደሎችንና ቃላትን በመመሥረት፣ በተገቢ የፊደላት አሰዳደር ሥርዓት ቃላትን በመጻፍና ሐሳብን በሥዕል ወይም በቃላት
በመግለጽ ላይ ያተኩራል። ተግባራቱም የሚከተሉትን ሊያካትቱ ይችላሉ፤
ƒƒ ፊደላትንና ቃላትን መጻፍ መለማመድን፤
ƒƒ ቃላትን በተገቢ ፊደላት አሰዳደር መሠረት መጻፍ መለማመድን፤
ƒƒ አጫጭር የቃል ጽሕፈትና የፊደላት አሰዳደር ፈተናዎች መፈተንን፤
ƒƒ ሐሳብን ለሌሎች ለማጋራት ዓረፍተነገሮችን መጻፍን።
ሳምንታዊ ትምህርቶቹ ማዕከል ያደረጉት ከአራቱ የቋንቋ ክሂሎች ማለትም ከማዳመጥ፣ ከመናገር፣ ከማንበብና ከመጻፍ ክሂሎች ጋር
በተቀናጀ ሁኔታ አምስቱን የማንብበ አላባውያንን ለመደገፍ የቀረቡ ጽሑፎችን በማዳመጥና በማንበብ ላይ ነው። የጽሑፎቹ ትኩረት
በየምዕራፎቹ የምንባብ ጭብጦችና ንኡሳን ርዕሰጉዳዮች ላይ ነው። የማዳመጥና የማንበብ ጽሑፎች አዳምጦና አንብቦ መረዳትን
ለማዳበር በጥቅም ላይ ውለዋል። በሌላ መልኩ ደግሞ ለማዳመጥና ለማንበብ የቀረቡ ጽሑፎች ለተማሪዎቹ ማዳመጥንና ማንበብን

viii
ለመለማመድ ሰፊ ዕድል የሚፈጥሩ ናቸው። ከጽሑፎቹ የሚገኙት ቃላት ደግሞ ለቃላትና ለትዕምርተድምጻዊ ግንዛቤ ተግባራት
ውለዋል። በጽሑፎቹ የተጠቀሱት ሃሳቦችም በሥዕል ለመወከል፣ ለመወያያነትና ለመጻፍ ተግባራት በጥቅም ላይ ሊውሉ ይችላሉ።
አምስተኛው ቀን ለሳምንቱ የተመደቡት የትምህርት ይዘቶች የሚከለሱበትና የተማሪዎች ችሎታ የሚገመገምበት ነው። በመሆኑም
በዚህ በአምስተኛው ቀን ተማሪዎች በሳምንቱ ውስጥ የተማሯቸውን ይዘቶች በተለያዩ መለማመጃዎች፣ ተግባራትና በትምህርታዊ
ጨዋታዎች ማለማመድ ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም በዚሁ በአምስተኛው ቀን የተወሰኑ ተማሪዎችን በመደበኛ ተከታታይ
ምዘና መርጦ መመዘን ያስፈልጋል። ይህም ምዘና ተማሪዎቹ ወደሚፈለገው የብቃት ደረጃ ማደግ ወይም አለማደጋቸውን ለመለካት
በአግባቡ ተመዝግቦ መያዝ አለበት።
የማስተማር መርሖች

ልሥራ፣ እንሥራ፣ ሥሩ
በዚህ ሥርዓተትምህርት ውስጥ ዋነኛው የማስተማሪያ ዘዴ በተለምዶ “ልሥራ፣ እንሥራ፣ ሥሩ” ወይም በትክክለኛ አጠራሩ “የመምህር
ሚናን ቀስበቀስ ለተማሪዎች የማስተላለፍ ሞዴል” (gradual release model) ተብሎ ይታወቃል። ተማሪዎች በመጀመሪያ ጥያቄዎች
ወይም ተግባራት በመምህር ሲሠሩ ያያሉ፤ ቀጥሎም የክፍሉ ተማሪዎች ከመምህራቸው ጋር አብረው በጋራ ይሠራሉ፤ በመጨረሻም
ራሳቸውን ችለው በግላቸው እንዲሠሩ የሚደረግበት የማስተማር ዘዴ ነው። ምንምእንኳ ሁሉም ደረጃዎች በሁሉም ቦታ ተሟልተው
የማይገኙበት ሁኔታ ቢኖርም፣ ሞዴሉ ለአብዛኛዎቹ የትምህርት ክንውኖች ወይም ተግባራት በዚህ የመምህር መጽሐፍ ውስጥ
በግልጽ ተብራርቶ ቀርቧል። ዘዴው ተማሪዎች አዳዲስ ክንውኖችን ወይም ተግባራትን ለመሥራትና በራስ የመተማመን አቅማቸውን
ለመገንባት ይረዳቸዋል።

በትብብር መማር
በትብብር መማር ተማሪዎች በቢጤ ወይም በቡድን ተደራጅተው ከክፍል ጓደኞቻቸው ጋር በመደበኛነት ወይም ለአጭር ጊዜ
ተወስነው የሚሰጧቸውን ተግባራት የመሥራት ዕድልን ይፈጥራል። ይህም ተማሪዎች ከጓደኞቻቸው ጋር አዳዲስ መረጃዎችን
የመለዋወጥ ዕድል ስለሚፈጥር የክፍል ውስጥ መማርን ያጠናክራል። በትብብር መማር ብዙ ተማሪዎች ባሉበት ክፍል ውስጥ
በንቃት እንዲሳተፉ ዕድል ይፈጥራል።

ግብረመልስ መስጠት
አንዱ የማስተማር ዋነኛ አካል ተማሪዎች በተናገሯቸው፣ ባነበቧቸው፣ ባቀረቧቸው ወይም በጻፏቸው ላይ ተመሥርተው የመምህር
ግብረመልስ መስጠት ነው። አንዳንድ ጊዜ ግብረመልስ ሳይሰጡ በሚሠሩ መለማመጃዎች ላይ ብቻ ማተኮር ጠቃሚ ሊመስል
ይችላል። ነገርግን ተማሪዎች የተሰጣቸውን ተግባር እንዴት መሥራት እንዳለባቸውና የሠሩትም ትክክል መሆኑን ወይም አለመሆኑን
ለመረዳት ስለሚጠቅማቸው ግብረመልስ መስጠት አስፈላጊ ነው። ግብረመልስ መስጠት ውጤታማ ይሆን ዘንድ መምህራን
የሚከተሉትን ማከናወን ይጠበቅባቸዋል፤
ƒƒ ተማሪዎች የሰጡት ምላሽ ትክክል ወይም ስህተት መሆኑን መንገር፤
ƒƒ ተማሪዎቹ የመለሱት መልስ ለምን ትክክል ወይም ስህተት ሊሆን እንደቻለ ማብራራት፤
ƒƒ በትክክል የተሠራውን ለተማሪዎች መንገር፤
ƒƒ የሚጠበቅባቸውን ተግባር በትክክል እንዴት መሥራት እንዳለባቸው ወይም ምን ዓይነት ብልሃት መጠቀም እንደላባቸው
መንገር።

ix
ተማሪዎች የሚነገራቸውን ትክክለኛ መልሶች ወይም አቀራረብ ከመስማት ይልቅ በራሳቸው ወደትክክለኛ መልስ እንዲደርሱ ወቅታዊ
ግብረመልስ በመስጠት ይታገዛሉ። ለምሳሌ፣ አንድ/ዲት ተማሪ አንድ አንቀጽ ሲያነብ/ስታነብ አንድ ቃል ሲጠራ/ስትጠራ ቢሳሳት/
ብትሳሳት በሚከተለው አኳኋን ሊነገረው/ ራት ይገባል፤ አንቀጹን ጥሩ አንበሃል/ሻል፤ ግን የኹለተኛው ዓረፍተነገር ኹለተኛ ቃል
“ቤቶች” ሳይሆን “ቤታችን” ነው፤ ስለ“-ኣችን” መማራችንን ታሳታውሳለህ/ሻለሽ? ወይም አንድ ተማሪ ከምንባቡ ውስጥ ያሉትን
ዋናዋና ነጥቦች እንዲዘረዝር/እንድትዘረዝር ለቀረበለት/ላት ጥያቄ የሰጠውን/ቺውን ምላሽ በማጤን፤ ከምንባቡ ዋናዋና ነጥቦች ውስጥ
ሁለቱን በትክክል መልሰሃል/ሻል፤ ጥሩ ነው፤ ሦስተኛው ነጥብ ምን እንደሆነ ልትነግረኝ/ሪኝ ትችላለህ/ቺያለሽ? ወዘተ።

የማስተማሪያ መርጃዎች
በብዙ አካበቢዎች የሚገኙ የመማሪያ ክፍሎች ለትምህርት አገልግሎት የሚውሉ ቁሳቁስ የተሟሉላቸው ናቸው ማለት አዳጋች ነው።
ስለዚህ በቀላሉ ባካባቢው ሊዘጋጁ የሚችሉ የማስተማሪያ መርጃ መሣሪያዎችን ለማዘጋጀት ጥረት ማድረግ ተገቢ ነው። ስለሆነም
ለዚህ ሥርዓተትምህርት ጠቃሚ ከሆኑት ቀላል የማስተማሪያ መርጃ መሣሪያዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙባቸዋል፤
ፍላሽ ካርዶች፡- ተማሪዎች የሚማሯቸውን ቃላት የሚያሳዩ ክርታሶች/ ካርዶች ናቸው። እነዚህ ካርዶች ቃላቱን ሰሌዳ ላይ ከመጻፍና
ያን እያጠፉ በመጻፍ ጊዜ ከማጥፋት በፍጥነት ካንዱ ፊደል ወይም ቃል ወደሌላው በቀላሉ እየለዋወጡ ለመጠቀም አመቺ ናቸው።
ከርቀት ለማንበብም ቀላል ስለሆኑ፣ ለሁሉም የክፍል ተማሪዎች፣ ለአነስተኛ ቡድኖች ወይም ለግል በቀላሉ ለመጠቀም ያመቻሉ።
በቀላሉም ቀደምብሎ ለማዘጋጀትና እንዳስፈላጊነቱ ደጋግሞ ለመጠቀም አመቺ ናቸው።
የመውጫ ካርዶች፡- እንደፍላሽ ካርዶች ተቆራርጠው የተዘጋጁ ስለሆኑ፣ ተማሪዎች እየጻፉባቸው ለመምህራቸው የሚያሳዩባቸው
ናቸው። ለምሳሌ፣ የማንበብ ሂደት ተግባራት እነዚህን ክርታሶች በመጠቀም ቢከናወኑ መልካም ነው።
ባለኪስ ሠንጠረዥ (Pocket-Chart)፡- የፖስተር መጠን ያለውና ከሸራ ወይም ከጨርቅ የተዘጋጀ ባለኪስ ሠንጠረዥ ሲሆን፣
ተማሪዎች እንዲያዩዋቸው ፍላሽ ካርዶችን ሊይዝ የሚችል ነው። ይህ ሠንጠረዥ በአንድ ጊዜ በርካታ ፍላሽ ካርዶችን ለማቅረብና
ለማሳየት እንዲሁም ከቦታ ወደቦታ በማዘዋወር ለመጠቀም ያመቻል። ዓረፍተነገሮችንም በአዳዲስ ቃላት ለመመሥረትና ስለቃላቱም
ፍቺ ለመነጋገር ያስችላል።
ትልልቅ መጻሕፍት፡- መምህራን ድምጽ በማሰማት ሲያነቡ፣ ሁሉም የክፍል ተማሪዎች ሊያዩዋቸው የሚችሉ በጣም ትልልቅ
መጻሕፍት ናቸው። ተማሪዎች ከነዚህ መጻሕፍት ቃላትን፣ ሥዕሎችን፣ ምሥሎችን፣ ሠንጠረዦችን ወዘተ. ሲያነቡ ስለርዕሰጉዳዩ
ያላቸውን ግንዛቤ ያዳብራሉ፤ ስለርዕሰጉዳዩም በአዲስና በተለየ መንገድ ለማሰብ ዕድል ይፈጥርላቸዋል። ከዚህ በተጨማሪ በመጽሐፉ
የቀረቡት መረጃዎች የቀረቡባቸውን መንገዶች ለመተንተን ያስችላቸዋል።
ሥዕላዊ መግለጫ (ፖስተር)፤ ለጭብጥና ለንኡሳን ርዕሰጉዳይ የሚዘጋጁ ሥዕላዊ መግለጫዎች (ለምሳሌ፣ በሥራቸው አርኣያ ስለሆኑ
ሴቶችና በማኅበረሰቡ ውስጥ ስላላቸው ሚና፣ ሰለአካባቢ ጥበቃ ዕቅድ፣ በተውኔት ውስጥ ቀርቦ ስለነበረ ወይም ወደፊት ስለሚቀርብ
ክፍል ወዘተ. የሚዘጋጁ) የተማሪዎችን ፍላጎትና ተሳትፎ ይጨምራሉ። መምህራን እነዚህን ሥዕላዊ መግለጫዎች ርስበርስ ሊለዋወጡ
ይችላሉ፤ ተማሪዎችም አዳዲስ ሥዕላዊ መግለጫዎችን በመፍጠር ረገድ ሊሳተፉ ይችላሉ።

የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሮች (Graphic organizers or semantic organizers)


ƒƒ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሮች ዲያግራሞችን ወይም ሌሎች ስዕልነክ መሣሪያዎችን በመጠቀም በቴክስት ውስጥ ጽንሰሐሳቦችንና
በጽንሰሐሳቦች መካከል ያለውን ቀጥተኛ ወይም ኢቀጥተኛ ትስሥር ምስል ፈጥረው ያሳያሉ፤
ƒƒ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሮች ተዋረዳዊ (hierarchical)፣ ፅንሰሀሳባዊ (conceptual)፣ ቅደምተከተላዊ (sequential)፣ ዙርመጥ
(cyclical) የሆኑ ማፖች፣ ድሮች፣ ቻርቶች፣ ፍሬሞች፣ ወይም ክላስተሮች ወዘተ፤ በሚሉ የተለያዩ ስሞችም ይጠራሉ።
ƒƒ የትርጉም ቢጋሮች (ሲማንቲክ ማፖች ወይም ሴማንቲክ ድሮች ይባላሉ)፤ የሸረሪት ድርመሰል የሆኑ የሐሳብ ማደራጃ
ቢጋሮች ናቸው።

x
ƒƒ በሴማንቲክ ቢጋር መስመሮች ቁልፍ የሆነውን ወይም ማዕከላዊዩን ሐሳብ ከተለያዩ ተዛማጅ ሐሳቦችና ድርጊቶች ጋር
ያገናኛሉ/ያስተሳስራሉ፤
ƒƒ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሮች አንባቢዎች በፅንሰሐሳቦች ላይና ፅንሰሀሳቦቹ ከሌሎች ፅንሰሐሳቦች ጋር እንዴት እንደተዛመዱ
ትኩረት እንዲያደርጉ ይረዳሉ።
ƒƒ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሮች አስረጂ ቴክስቶችን፣ እንደሣይንሥና የማህበራዊ ሣይንሥ እንዲሁም የንግድ መማሪያ መጽሐፎችን
ለመማር ማንበብ ያግዛሉ።
ƒƒ በአስረጂ ጽሑፎች ላይ ጥቅም ላይ ሲውሉ፣ የሐሳብ ማደረጃ ቢጋሮች ፅንሰሐሳቦች የሚጋሯቸውን ቴክስታዊ መዋቅር
ለመረዳት ተማሪዎችን ያግዛሉ።
ƒƒ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሮች በተራኪ ታሪኮች የታሪኮችን መዋቅር ለማመላከት ተግባራዊ ይሆናሉ።
ƒƒ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋር በተጨማሪም ለተማሪዎች፣
ƒƒ በሚያነቡበት ጊዜ በታሪክ ወይም በምንባብ መዋቅር ላይ እንዲያተኩሩ ያግዛል፤
ƒƒ በሚያነቡት ቴክስት ዝምድናዎችን ለማየትና ለመመርመር የሚረዱ መሣሪያዎችን ይሰጣል፤
ƒƒ ታሪክ ወይም ምንባብ አንብበው በትክክል የተደራጀና የተዋቀረ ማጠቃለያ ለመጻፍ ይረዳቸዋል፤

ተከታታይ ምዘናና ድጋፍ/ማበልፀግ


ተከታታይ ምዘና ተማሪዎች እንዴት እየሠሩ እንደሆነና ትምህርቱን መረዳታቸውንና ክሂሎችን በሚፈለገው መጠን ማወቃቸውን
ለመረዳት በተከታታይ መረጃ የሚሰበሰብበትና የሚተነተንበት ሂደት ነው። ምዘናው ስለማስተማር ሂደት ወይም ሊከለሱ
ስለሚገባቸው ወይም በድጋሚ ማስተማር ስለሚያስፈልጋቸው ትምህርቶች ውሳኔ ለመስጠት ስለሚያስችል ለመምህራን በጣም
ጠቃሚ ነው። በተጨማሪም ተማሪዎች በመንፈቀዓመቱ ውስጥ ከሚጠበቁባቸው ብቃቶች አንጻር የሚያሳዩትን ዕድገት በሚመለከት
ያላቸውን ምልከታና የተከታታተይ ምዘና ወጤቶችን ለመመዝገብ መምህራን ሊጠቀሙበት ይችላሉ።
ተማሪዎች እንዴት እየሠሩ እንደሆነ በተከታታይ ምዘና ለመረዳት፣ በመማር ሂደት ውስጥ ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች ለመርዳትና
ጥሩ ለሚሠሩትም ዕውቀታቸውን ለማበልፀግ ለመምህራን የሚከተሉት ኹለት ዓይነት አጠቃላይ የምዘና ስልቶች (ቴክኒኮች)
ጠቃሚዎች ናቸው።

ኢመደበኛ ተከታታይ ምዘና


ኢመደበኛ ተከታታይ ምዘና የመማር ማስተማሩን ሂደት የተማሪዎችን መማር እግርበግር እየተከታተሉ፣ ጕድለት ካለ ለመሙላትና
ድጋፍ ለማድረግ ታልሞ የሚተገበር ምዘና ነው። በዚህ ረገድ ከሚጠቀሱት ዘዴዎች ቀጥሎ የቀረቡትን መጠቀም ይቻላል፡-
ƒƒ ምልከታ፡- መምህራን “እንሥራ” በተለይ ደግሞ “ሥሩ” በሚለው የትምህርቱ ሂደት ወቅት በክፍል ውስጥ በመዘዋወር
ተማሪዎቻቸውን መከታተል አለባቸው። በዚህ ጊዜ ተማሪዎቹ በግላቸው፣ ከቢጤያቸው ወይም ከአነስተኛ ቡድን ጋር
እንዴት እየሠሩ እንደሆነና የትኞቹ የተለየና ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚፈልጉ፣ የትኞቹ ደግሞ የተሻለ ለመሥራት ከአቅማቸው
ጋር የሚሄድና የሚገዳደራቸው ተግባር እንደሚፈልጉ መምህራን ለመለየት ይችላሉ።
ƒƒ የመውጫ ካርዶች፡- የዕለቱ ትምህርት ከመጠናቀቁ በፊት መምህራን ለተማሪዎች ጥያቄ ሊጠይቁ ወይም አጭር ተግባር
ሊሰጡ ይችላሉ። ለምሳሌ፣ ለቃላት ተመሳሳይ እንዲሰጡ፣ ከተማሯቸው ቃላት የተወሰኑትን ዓረፍተነገር በመመሥረት
እንዲጠቀሙ ወይም ለአጭር አንቀጽ ማጠቃለያ እንዲሰጡ ወዘተ. የመሳሰሉትን መጠየቅ ይቻላል። ተማሪዎቹም
ምላሾቻቸውን በቁራጭ ወረቀት ወይም ካርድ ላይ በመጻፍ ለመምህራቸው ሰጥተው ይወጣሉ። ከዚያም መምህራኑ ያን
በመመልከት ምን ያህሉ ተግባሩን በትክክል መሥራት እንደቻሉ መገምገም ይችላሉ።

xi
ƒƒ ተነሺ ቃላት፡- ተማሪዎች በትናንሽ ሰሌዳዎች ወይም ወረቀቶች ላይ መልሶችን ጽፈው፣ መምህራቸው ጥያቄዎችን
በግላቸው (ለምሳሌ፣ ጥያቄ መጠየቅ፣ መልስ መመለስ፣ በቃላት ዓረፍተነገር መሥራት) እንዴት እንደመለሱ እንዲያዩላቸው
በፊትለፊታቸው በጠረጴዛቸው (በዴስካቸው) ላይ ያስቀምጣሉ።

መደበኛ ተከታታይ ምዘና


የዚህ ምዘና ዋና ዓላማ ተማሪዎች ትምህርቱን መረዳታቸውንና ክሂሎችን በሚፈለገው መጠን ማወቃቸውን በየደረጃውና በየምዕራፉ
መጨረሻ መለካት ነው። የሚከተሉትን ዘዴዎች ለአብነት መጠቀም ይቻላል፤
ƒƒ የክፍል ልምምዶችና የቤት ሥራዎች፡- መምህራን፣ ትምህርቱን መረዳታቸውንና ክሂሎች በተገቢው ሁኔታ መዳበራቸውን
ለመረዳት ተማሪዎች በጽሑፍ የመለሷቸውን የክፍልና የቤት ሥራዎች ሰብስበው ይገመግማሉ።
ƒƒ ሙከራዎችና ፈተናዎች፡- ተማሪዎች አንድን የትምህርት ይዘት ወይም ክሂል መረዳታቸውን ለማወቅ ሙከራዎችና ፈተናዎች
ሊሰጡ ይችላሉ። ከ5ኛ-8ኛ ባሉት የክፍል ደረጃዎች የሚሰጡት ሥራዎችና ፈተናዎች በአብዛኛው በጽሑፍ የሚመለሱ
ናቸው። ይሁንና ፈተናዎች በቃል የሚመለሱም ሊሆኑ (ለምሳሌ፣ የአቀላጥፎ ማንበብ ችሎታቸውን ለመለካት ከአንድ
ጽሑፍ የተወሰነውን ድምጽ በማሰማት እንዲያነቡ ወይም የአንብቦ/ የአዳምጦ መረዳት ችሎታቸውን ለማወቅ ጥያቄዎችን
በቃላቸው እንዲመልሱ ወይም ስለአንድ ጉዳይ በቃላቸው እንዲያቀርቡ ማድረግ) ይችላሉ።
ድጋፍ ምን ማለት ነው? ድጋፍ፣ መምህራን ተማሪዎችን ለማበረታታት የሚፈጸሙት ተግባር ወይም የሚሰጡት የማበረታቻ ቃል
ነው።
አንዱ የተከታታይ ምዘና አስፈላጊነት ተጨማሪ ድጋፍ የሚፈልጉ ተማሪዎችን ለመለየት ነው። ይህም በእንሥራና በተለይ በልሥራ
ልምምድ ወቅት መምህራን ትምህርቱን ለመገምገምና ችግር ላለባቸው ተማሪዎች በወቅቱ ድጋፍ ለማድረግ ዕድል ይሰጣቸዋል።
አንዳንድ ጊዜም ከክፍል ውጪ ድጋፍ የሚሹ የተወሰኑ ተማሪዎች ሊያጋጥሙ ይችላሉ።
ƒƒ ለክፍሉ፣ ለአነስተኛ ቡድን ወይም በግል ድጋፍ ለሚፈልጉ ተማሪዎች ድጋፍ የማድረጊያው አንዱ መንገድ ወደልሥራ ወይም
ወደእንሥራ ተመልሶ የተማሩትን ይዘት ወይም ክሂል ተጨማሪ ምሳሌዎች እየሰጡ ማለማመድ ነው።
ማበልፀግ ምን ማለት ነው? አንዳንድ ተማሪዎች ፅንሰሐሳብን ቶሎ ሊረዱ ስለሚችሉ ትኩረታቸውን ለመያዝ የሚገዳደራቸው
ነገር ይሻሉ። ማበልፀግ የሚያመለክተው ለእንደነዚህ ያሉ ተማሪዎች ተጨማሪ መረጃ በማቅረብ ያላቸውን ዕውቀት የሚያሰፋና
የሚያዳብር ተግባር መስጠትን ነው። በዚህም ተማሪዎች በአዲስ መልክ የቀረቡላቸውን መረጃዎች እንዲጠቀሙባቸው በማድረግ
ዕውቀታቸውን እንዲያሰፉ መገዳደር ይቻላል።
በተከታታይ ምዘና ሂደት የቀረበው ተግባር ወይም ክሂል የሚቀላቸውንና ከበድ ያለ ተግባር ወይም ክሂል የሚያስፈልጋቸውን
ተማሪዎች ለይቶ ማወቅ ይቻላል። የነዚህን ተማሪዎች ዕውቀት ማበልፀግ ካልተቻለ በትምህርቱ ሊሰላቹና ፍላጎት ሊያጡ ወይም
የተለየ ባሕርይ ሊያሳዩና ችግር ሊፈጥሩ ይችላሉ።
ለእነዚህ ተማሪዎች የማበልፀጊያ ተግባር የሚሰጠው በኹለት ዓይነት መንገድ ነው፤ አንደኛው ተጨማሪ የማንበብ ተግባር
(ከመጽሐፋቸው ሌላ ተጨማሪ አጋዥ መጽሐፍ እንዲያነቡ) እና ኹለተኛው ተጨማሪ የመጻፍ ተግባር (በመጽሐፋቸው ውስጥ የሌለ
ሌላ የመጻፍ ሥራ) መስጠት ናቸው። ምናልባት በተጨማሪ የሚነበቡ ጽሑፎች ወይም መጻሕፍት ከሌሉ፣ መምህራን በተማሪዎች
መማሪያ መጽሐፍ ውስጥ ያሉትን የሚመስሉ የመጻፍ ተግባራት ሊያዘጋጁ ይችላሉ። ከዚያም ላቅ ያለ ችሎታ ያላቸው ተማሪዎች
አንዳቸው የአንዳቸውን ሥራ እንዲያነቡና ግብረመልስ እንዲሰጣጡ፣ አርትኦት እንዲያደርጉ፣ በሥራዎቻቸው ላይ እንዲወያዩ ወዘተ.
ማድረግ ይቻላል። ይህም ተጨማሪ ንባብ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል። አንዳንድ ጊዜ መምህራን ተማሪዎችን በማቧደን የአፈጻጸም
ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች ጥሩ አፈጻጸም ካላቸው የሚማሩበትንም መንገድ ሊያመቻቹ ይችላሉ።

xii
ሥርዓተፆታና አካቶ ትምህርት

ሥርዓተፆታን ከግምት ውስጥ ያስገባ ማስተማርና መማር


መምህራን ወንድና ሴት ተማሪዎች እኩል የሚሳተፉበትና የሚጠቀሙበት የመማር አካባቢ መፍጠር አለባቸው። ስለሥርዓተፆታ በቂ
ግንዛቤ የሌላቸው መምህራን በክፍል ውስጥ አዘውትረው የሚጠሩት፣ ከባድ ጥያቄዎችን የሚጠይቁት፣ ለቡድን መሪነት የሚመድቡት
ወንድ ተማሪዎችን ብቻ ነው። እንዲህ ዓይነቱ ወዳንድ ፆታ ያደላ አቀራረብ የሴቶችን የትምህርት ተሳትፎ፣ ውጤት፣ የወደፊት
ችሎታና ተስፋ በእጅጉ ይጎዳል።
ስለሆነም የሁለቱንም፣ የሴቶችንና የወንዶችን ተማሪዎች የትምህርት ውጤት ለማሳደግና የሥርዓተፆታ እኩልነት የሰፈነበት
ሥነትምህርት በክፍል ውስጥ ለመጠቀም ይችሉ ዘንድ መምህራን ራሳቸው መማር አለባቸው። ከግምት ውስጥ ሊገቡ ከሚገባቸውና
ማስተማርንና መማርን የሥርዓተፆታ እኩልነት የሚንፀባረቅባቸው ለማድረግ ከሚጠቅሙ ጉዳዮች መካከል የሚከተሉት
ይገኙባቸዋል፤
ƒƒ የማስተማሪያና የመማሪያ መሣሪያዎች፡- መምህራን የትምህርት መሣሪያዎችን ከሥርዓተፆታ እኩልነት አንፃር የወንድና የሴት
ገፀባሕርያትን ውክልናና ሥዕሎችን መገምገም አለባቸው። በተማሪ መጽሐፉ ምንባቦች ውስጥ የወንድና የሴት ገፀባህርያት
ውክልና ተመጣጣኝ እንዲሆንና በሥዕሎችም ረገድ የሥርዓተፆታ ሚዛናዊነት እንዲኖር ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል።
በዚህም መሠረት በጽሑፎችና በሥዕሎች ውስጥ ልጃገረዶች/ሴቶች ወንዶች ልጆች/ወንዶች ጐልማሶች በተመጣጠነ
ሁኔታ እንዲወከሉ ተደርጓል። በቋንቋ አጠቃቀም ረገድም እንዲሁ የሥርዓተፆታ ወገናዊነት ሳይኖር፣ ሁለቱንም ፆታዎች
በእኩልነት በሚያማክል አገላለጽ ለመጠቀም ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል። ለዚህም ሲባል ገፀባህርያቱ በቤት ውስጥም ሆነ
በአደባባይ በሚኖራቸው የተግባር ተሳትፎ ሚዛናዊነት እንዲኖራቸው ከመደረጉም በላይ ሥርዓተፆታነክ የሆኑ ጭብጦችና
ንኡሳን ርዕሰጉዳዮች፣ ለምሳሌ፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች፣ ሴቶችን ማጐልበት፣ ሥርዓተፆታና ትምህርት ወዘተ. የሚሉ
ተካትተውበታል። ይሁንእንጂ፣ ምናልባት በስህተት የተዘለለና የነበረው የሥርዓተፆታ አድሎ የሚንጸባረቅበት ጽሑፍ
ካጋጠመ፣ መምህራን አስተካክለው ያለውን ክፍተት እንዲሞሉ ይጠበቃል። አካላዊ ቋንቋ በሚጠቀሙበት ጊዜም የዚያኑ
ያህል ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። ሁሉንም ተማሪዎች በማበረታታት ሴት ተማሪዎች በራስ የመተማመን መንፈስ
እንዲያድርባቸው ማድረግም እንዲሁ ትኵረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው።
ƒƒ የክፍል ውስጥ አደረጃጀት፡- የክፍል ውስጥ የመቀመጫ አቀማመጥ ሥርዓተፆታን ከግምት ውስጥ ያስገባ መሆን አለበት፤
ለምሳሌ፣ የሴት ተማሪዎች ወደኋላ ባሉት መቀመጫዎች መቀመጥ ለክፍል ውስጥ ተሳትፏቸው ችግር ይፈጥራል። ስለሆነም
መምህራን በቡድን የተከፋፈለ አቀማማጥ እንዲኖር ወይም የተለየ መንገድ ፈልገው ሁሉም ተማሪዎች እንዲሳተፉ ለማድረግ
የተሻለ ሥርዓተፆታን ያማከለ አቀማመጥ መፍጠር ይኖርባቸዋል።
ƒƒ የክፍል ውስጥ መስተጋብር፡- በክፍል መስተጋብር ጊዜ መምህራን ለሁሉም ሴትና ወንድ ተማሪዎች እኩል ዕድል
መስጠታቸውን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ፣ በክፍል ውስጥ ስም በሚጠሩበት ጊዜ በተመሳሳይ መጠን ሁለቱንም
ፆታዎች እኩል በመጥራት ማሳተፍ ይገባል። በማበረታቻም ሆነ በግብረመልስ አሰጣጥ ሁለቱም ፆታዎች ተገቢ ትኵረት
ማግኘታቸውንም ማረጋገጥ አስፈላጊ ነው። የተለያዩ ባሕርያትን እንዲላበሱ ወይም ወክለው እንዲከውኑ ሲደረግም
ከተዘወተረው የተዛባ አመለካከት በፀዳ መልክ ትኵረት ሰጥቶ በእኩልነት ማከፋፈል ይገባል።
በመተግበር ላይ ካለው ርዕሰጉዳይ ጋር በተገናኘ በክፍል ውስጥ ሥርዓተፆታነክ ጉዳይ ሲነሳም፣ መምህራን ለአንዱ ሳይወግኑ ተገቢ
ትኵረት ሰጥተው በሚዛናዊነት ማስተናገድ ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች፤ የሚለው ርዕሰጉዳይ በሚነሳበትና
በዚህ ላይ ውይይት በሚደረግብት ጊዜ መምህራን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች በሴቶች ላይ ስላደረሱትና ስለሚያደርሱት ጉዳት ትኵረት
ሰጥተው ማብራራትና የተማሪዎቹም ተግባር እንዲህ ዓይነቱን ጎጂ ድርጊት ማስወገድ መሆን እንዳለበት ማስረዳት ይኖርባቸዋል።

xiii
ƒƒ ለአካለመጠን መድረስ፡- ልጆች፤ ወንዶችም ሆኑ ሴቶች እያደጉ ሲመጡ በትምህርታቸው ላይ ተጽዕኖ ሊኖራቸው የሚችሉ
አካላዊና ሥነልቦናዊ ለውጦች ማሳየታቸው አይቀሬ ነው። ሴቶች በወር አበባቸው ወቅት በሚሰማቸው የህመም ስሜት
የተነሳ ከክፍል እስከመቅረት ሊደርሱ ይችላሉ። ይህ በሚሆንበት ጊዜ መምህራን የተቋረጠባቸውን ትምህርት፣ ጊዜ
ሰጥተውና የማካካሻ መርሐግብር አውጥተው ማስተማር ይኖርባቸዋል። ወንዶች ልጆችም እንዲሁ በሚጎረምሱበት ወቅት
ለትምህርታቸው ትኵረት ላይሰጡና በራሳቸው ላይ ስላለው ለውጥ ብቻ ሊያስቡ ይችላሉ። በመሆኑም መምህራን ይኼን
ለውጥ ተገንዝበው ተገቢውን ድጋፍና ምክር ለሁለቱም ፆታዎች መስጠት ይጠበቅባቸዋል።
ƒƒ ወሲባዊ ትንኮሳ፡- ወንዶችንም ሆነ ሴቶች ተማሪዎችን በአካል፣ በሥነልቦናና በስሜት እንደሚጎዳ ተገንዝበው፣ መምህራን
በምንም ሁኔታ ወሲብነክ የሆነ አስተያየት ከመስጠት፣ አካላዊ እንቅስቃሴ ከማድረግ፣ አልፎተርፎም ትንኮሳ ከማድረግ
መቆጠብ አለባቸው። እንዲህ ዓይነቱም ተግባር በራሳቸው በተማሪዎችም ቢሆን እንዳይፈጸም መከላከል አለባቸው።

አካቶ ትምህርት
አንዳንድ ተማሪዎች ለትምህርት ተደራሽ ለመሆንና በእኩልነት የትምህርት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ የተለየ ተጨማሪ ድጋፍ
የሚሹ ይሆናሉ። ይህ የሚሆነው ልጆች ባለባቸው አካል ጉዳተኝነት ምክንያት (ውሱን የመማር፣ የመስማት፣ የማየት፣ ዕድገት/
ውስንነት፣ የቋንቋ ወይም የመንተባተብ፣ የኦቲዝም፣ የአእምሮ ጉዳት፣ የመስማትና የማየት ወይም የተለያዩ የአካል ጉዳተኛነት
ችግሮች) ሊሆን ይችላል። በተጨማሪም ከክፍል ደረጃቸው በላይ የአእምሮ ብስለት ወይም የመፍጠር ችሎታም ባላቸው ተማሪዎች
ዘንድም ሊከሰት የሚችል ችግር ነው።
ስለዚህ ችግሮችን ለመቅረፍ በዚህ የመምህር መጽሐፍ ውስጥ የተለያዩ የማስተማሪያ ስልቶች ተካትተዋል። በመሆኑም መጽሐፉ
የተለያዩ የማስተማሪያ ዘዴና የተለያዩ የተግባራት አቀራረቦች፣ የሚታዩ፣ የሚደመጡ፣ የሚዳሰሱ፣ የሚሞከሩ ተግባራትን በማካተት
ተማሪተኮር የሆነ አጠቃላይ መርሕ የተከተለና ተከታታይ ምዘናን ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው። ከዚህ በተጨማሪ ይህ ክፍል የልዩ
ፍላጎት ተማሪዎችን ለማገዝና ለመደገፍ በክፍል ውስጥ ሊተገበሩ የሚችሉ አጠቃላይ ስልቶችን ያቀርባል። ትኵረት የተሰጠውም
የማስታወስ፣ የተግባቦት፣ የቃላት ዕውቀትና የቋንቋ ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች የበለጠ በማገዝ ላይ ነው። አንዳንዶቹን ችግሮች
ለመቅረፍ የሚከተሉትን መተግበር ይጠቅማል፣
ƒƒ መመሪያን ወይም ትዕዛዝን በራሳቸው ቋንቋ መልሰው እንዲሉት ተማሪዎችን መጠየቅ፤ ይህ የመረዳትና የመመለስ ችግር
ላለባቸውና መመሪያው ላመለጣቸው ተማሪዎች በጣም ጠቃሚ ነው። መመሪያውን ደግሞ የመናገሩን ተግባር ለቢጤያቸው
ወይም ለመምህር ሊያቀርቡ ይችላሉ። መምህራንም በአንድ ጊዜ የሚሰጧቸውን የቃል መመሪያዎች ቊጥር መወሰን
ይኖርባቸዋል።
ƒƒ የፅንሰሐሳብና የስልተትግበራ ግምገማዎች መስጠት፤ እያንዳንዱን ቀን በቀደመው ክፍለጊዜ የተማሯቸውን ክሂሎችና
ሐሳቦች በመከለስ መጀመር ይቻላል። የቀደሙ ትምህርቶች ዕለታዊ ግምገማ ተማሪዎች አዲሱን ትምህርት ከቀደመ
እውቀታቸው ጋር ለማገናኘት ይጠቅማቸዋል።
ƒƒ የተለያዩ የመገናኛ መንገዶችን (የዓይነተብዙ ፍንጮች) መጠቀም፤ በተቻለ መጠን መረጃዎች በተለያየ መንገድ ለምሳሌ፣
በሚደመጡ፣ በሚታዩ፣ በሚዳሰሱ፣ በእንቅስቃሴ በሚታገዙ ዘዴዎች ለማቅረብ መሞከር ጥሩ ነው። ለምሳሌ፣ መዝሙሮችን
ከአካል እንቅስቃሴ ጋር አንድ ላይ መጠቀም ይቻላል።
ƒƒ የዕለት ዝውትሮችን/ክንዋኔዎችን አለመለዋወጥ፤ የመማር ችግር ያለባቸው በርካታ ተማሪዎች እነዚህን የየዕለት ዝውትሮችን
ለማወቅና ምን እንደሚጠበቅባቸው ለመረዳት ይጠቀሙባቸዋል። ስለዚህ እነዚህን ዝውትሮችና የሚጠበቁባቸውን
ትምህርታዊ ግቦች በሰሌዳ፣ በግድግዳ ወይም በጠረጴዛቸው ላይ መጻፍ ወይም መለጠፍ ይጠቅማል።
ƒƒ ለተግባራትና ለተማሪዎች ሥራዎች የበለጠውን ጊዜ መመደብ፤ አንዳንድ ተማሪዎች አዳዲስ መረጃዎችን ለማጤን፣ ከራስ
ጋር አዋህዶ ለማቆየትና አዲሱን ዕውቀትና ክሂል ለመጠቀም ረዘም ያለ ጊዜ ሊወስድባቸው ይችላል። በመሆኑም ተግባሩንና

xiv
የተሰጣቸውን ሥራ እንዲጨርሱ በቂ ጊዜ መስጠት አስፈላጊ ሊሆን ይችላል። የሚሰጣቸውንም የሥራ መጠን መቀነስ
አስፈላጊ ሊሆን ይችላል። ለምሳሌ፣ ጥቂት ዓረፍተነገሮችን ወይም ቃላትን ሰጥቶ እንዲያነቡ ማድረግ አንዱ መንገድ ነው።
ƒƒ ምንባቡን መከታተል የማይችሉ ከሆነ የሚሰጡ መመሪያዎችን በሰሌዳ መጻፍ፤ በተለይ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ
መስማት የማይችሉ ተማሪዎች ሲኖሩ የሚተላለፉ መመሪያዎችን፣ ቊልፍ ዕሳቤዎችንና ቃላትን ሰሌዳ ላይ መጻፍ አስፈላጊ
ነው። ከዚህ ጋር የተያያዘ በክፍል ውስጥ ተገቢ የሆነ መቼት መፍጠር ለምሳሌ፣ የድምጽ ማስተጋባትና የመቆራረጥ ችግር
እንዳይኖር በማድረግ በመምህርና በተማሪዎች መካከል ለሚኖረው ተግባቦት አመቺ ሁኔታ መፍጠር ይገባል። አስፈላጊ
ሲሆንም የማዳመጡን ምንባብ አባዝቶ መስጠት፣ ሥዕሎችንና የሚታዩ ተጨባጭ ነገሮችን በድጋፍ መልክ መጠቀም
ጠቃሚ ነው።
ƒƒ መመሪያዎችን በቃል ማንበብ፣ ጽሑፎችን ማጕላት፤ የማየት ችግር ላለባቸው ተማሪዎች መምህራን ለሌሎች ተማሪዎች
በሰሌዳ ላይ እየጻፉ እያሉ ለእነዚህ ተማሪዎች መመሪያዎችን ጮክ ብለው ያንብቡላቸው፤ ወደሰሌዳው ጠጋ ብለው
እንዲቀመጡም ይፍቀዱላቸው፤ ከተቻለም መመሪያዎችን በጕልህ ጽፈው በሚታይ ቦታ ሊያደርጉላቸው ይችላሉ።
ƒƒ በመደጋገፍ የመማርና የቢጤ መማማር ዘዴን መጠቀም፤ ተመሳሳይ ወይም የተለያየ ችሎታ ያላቸውን ተማሪዎች በቡድን
አዋቅሮ ርስበርስ እንዲማማሩ ማድረግ ጠቃሚ ነው። በተማሪዎችም መካከል መተዋወቅንና መከባበርንም ይፈጥራል፤
በራስ የመተማመንን ስሜትና ማኅበራዊ ክሂል ያዳብራል። መምህራን ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች ለትምህርቱ ሂደት
አስተዋጽዖ እንዳላቸውና የነቃ ሚና እንደሚጫወቱ ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል።
ƒƒ አንድ ተግባር ተሠርቶ ካለቀ በኋላ ግልጽ፣ ወቅታዊና አዎንታዊ ግብረመልስ መስጠት፤ የልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ከሌሎቹ
ተማሪዎች እኩል በተመሳሳይ ፍጥነት ላይማሩ ይችላሉ። ይህም ራሳቸውን ከሌሎቹ ያነሱ አድርገው እንዲቆጥሩ
ሊያደርጋቸው ይችላል፤ ለትምህርት ያላቸውን ተነሳሽነትና የመማር አቅምም ሊጎዳው ይችላል። በመሆኑም ያሳዩት መሻሻል
ጥቂት እንኳ ቢሆን አዎንታዊ የሆነ አበረታች ግብረመልስ መስጠት መዘንጋት የለበትም።
ከላይ የተዘረዘሩትን ስልቶች በሚገባ ለመተግበር መምህራን የተማሪዎቻቸውን ፍላጎትና ችሎታ መረዳት ይኖርባቸዋል።
በትምህርትቤት ውስጥ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ሥልጠና ያላቸው መምህራን ካሉ ከነሱ ጋር በመሆን በጋራ በመሥራት የተማሪዎቹን
ፍላጎቶች መለየትና በትምህርቱም ሂደት ለማካተት መሞከር ያስፈልጋል።

የመምህር መጽሐፉ አጠቃቀም


ይህ የመምህር መጽሐፍ ለተማሪ የተዘጋጀውን የተማሪ መጽሐፍ ደረጃ በደረጃ ይከተላል። ለምዕራፎች፣ ለሳምንታትና ለቀናት የተሰጡ
መለያ ቊጥሮች ከተማሪ መጽሐፍ ጋር አንድ ናቸው። እያንዳንዱ ምዕራፍ የሚጀምረው በምዕራፉ ዓላማዎች ነው።
ለእያንዳንዱ የትምህርት ይዘት የመምህር መጽሐፉ የሚከናወኑ ተግባራትን አስፈላጊ ሲሆን በልሥራ - እንሥራና - በሥሩ
አቀራረብ መንገድ አዘጋጅቶ አቅርቧል። የትምህርቱንም ሂደት ቀላል ለማድረግና ተግባራቱንም ለማመቻቸት ለመምህራን በጣም
ግልጽና ተጨባጭ መመሪያዎችን ይሰጣል። ከጥቂት ሳምንታት ማስተማር በኋላ መምህራን ከተለያዩ ተግባራት ጋር ስለሚተዋወቁ
የሚሰጧቸው መመሪያዎች ያጥራሉ፤ ነገርግን ሁልጊዜ መምህራን እያንዳንዱን ተግባር እንዴት መተግበር እንዳለባቸው ወደኋላ
ተመልሰው የቀደሙትን ሳምንታት መመሪያዎች መመልከት ይጠበቅባቸዋል።

አጻጻፍን በሚመለከት በጥቅም ላይ የዋሉ ማሻሻያዎች


በአማርኛ ቋንቋ አጻጻፍ ረገድ አንድ ወጥ የሆነ ስምምነት የለም። በዚህም ምክንያት መምህራን ትኵረት ሰጥተው በራሳቸው
ለመጠቀምም ሆነ ለማስተማር ሲቸገሩ ይታያሉ። በመሆኑም ችግሩን በመቅረፍ ተማሪዎችን በተመሳሳይና ወጥ በሆነ መንገድ
ለማስተማር በአዳዲሶቹ የመምህርና የተማሪ መጻሕፍት ውስጥ ትኵረት ከተሰጣቸው ትምህርታዊ ጉዳዮች አንዱ እንዲሆን ተደርጓል።
በዚህም መሠረት የሚከተሉት ማሻሻያዎች ተደርገዋል፤

xv
ሀ. እንደትምህርትቤት፣ ዳቦቤት፣ መሥሪያቤት ወዘተ. ያሉት ጥምር ቃላት በመሆናቸው በወጥነት አንድ ላይ ተጠጋግተው
እንዲጻፉ ተደርገዋል፤ መምህራን ትኵረት ሰጥተው ራሳቸውም በጥንቃቄ እየተጠቀሙ ለተማሪዎቻቸው እንዲያለማምዷቸው
ያስፈልጋል።
ለ. እንደቅድመንባብ፣ ድኅረንባብ፣ ኅብረተሰብ፣ ቅድመማዳመጥ ወዘተ. ያሉ ባለአጣማሪ (-ኧ-) ቃላትም በተዘበራረቀ መንገድ
መጻፋቸውና በትምህርት አሰጣጣችንም ሆነ በአጻጻፍ ሥርዓታችን ላይ ችግር መሆናቸው የቆየ ጉዳይ ነው፤ ስለዚህ በአሁኖቹ
መጻሕፍት ውስጥ አንድ ላይ ተጠጋግተው እንዲጻፉና መምህራን ራሳቸው በጥንቃቄ እየተጠቀሙ ለተማሪዎቻቸው
እንዲያስተምሩ ይጠበቃል።
ሐ. ሌላው እዚህ ላይ የሚጠቀስ ማሻሻያ በመስተዋድዳዊ ሐረግ ውስጥ መስተዋድዱንና አብረዋቸው የተዋቀሩትን ስማዊ ሐረጎች
በተዘበራረቀ መንገድ ከመጻፍ በወጥነት ለመጠቀም የተደረገው ሙከራ ነው። እንደሚታወቀው መስተዋድዳዶችን ስ-፣ ስለ-
እንደ-፣ እንድ-፣ ወደ-፣ እስከ- ወዘተ. በሙሉ ማለት በሚቻልበት ሁኔታ (ዘንድ የሚለው መኖሩን ሳንዘነጋ) ራሳቸውን ችለው
ለብቻቸው መቆም የሚችሉ አለመሆናቸውን በሰዋስው እያስተማርን፣ አብዛኞቻችን ስንጽፍ ግን ልክ ራሳቸውን እንደቻሉት
ቃላት በኹለት ነጥብ እየለየን ነው። ይሁንና በነዚህ አዳዲስ መጻሕፍት ውስጥ በወጥነት፣ ለምሳሌ፣ እንዲበላ፣ እንደመጣ፣
እንደአባቱ፣ ወደትምህርትቤት፣ ስለመጣ፣ ስለአበበ፣ ስበላ፣ ሲበላ፣ ከቤቱ በላይ፣ ወዘተ. የሚሉት አንድ ላይ እንዲጻፉና
ትምህርቱም በዚሁ ዓይነት እንዲሰጥ ተዘጋጅቷል።
መ. ሌላው ትኵረት የሚሻ ጉዳይ የብዙ ቊጥር ቃላትን የምንጽፍበት ሥርዓት ነው። እንደሚታወቀው ቃላትን ወደብዙ ቊጥር
የምንለውጥባቸው መንገዶች እንደቃላቱ ክፍል የተለያዩ ቢሆኑም፣ በተለይ በስሞች ላይ የሚታየው ወጥነት የጎደለው ይመስላል።
ለምሳሌ፣ ቃል ብሎ ቃላት ወይም ቃላት ማለት ሥርዓት የተከተለ ሲሆን፣ ቃላቶች ማለት ግን ብዙ ቊጥርን የሚያመለክተውን
ቃል እንደገና የብዙ ቊጥር ምዕላድ ጨምሮ (ቃል + -ኣት= ቃላት + -ኦች= ቃላቶች) ማብዛትን የሚያሳይ የተዘወተረ ግድፈት
ነው። በመሆኑም በወጥነት በአንዱ መንገድ ማለትም በአማርኛው የብዙ ቊጥር ምዕላድ -ኦችን (ከነዘሮቹ) መጠቀምና ቃላት፣
መምህሮች፣ ሕፃኖች፣ ዕፆች ወዘተ. እያሉ፣ አለበለዚያም ከግእዝ ቋንቋ ወስደን በምንጠቀምበት የብዙ ቊጥር ሥርዓት፣ ቃላት፣
መምህራን፣ ሕፃናት፣ ዕፅዋት ወዘተ. በማለት መጻፍና ይህንኑም ለተማሪዎች በወጥነት ማስተማር በጣም አስፈላጊ ሆኗል።
ከዚህ በተለየ ግን መምህራኖች፣ ቃላቶች፣ ዕፅዋቶች እያሉ መጠቀም (በቋንቋው ውስጥ መነሻ ምክንያት ያለው ቢመስልም)
ሥርዓታዊም ተገቢም አይመስልም፤ እንደትልቅ ሕፀፅ የሚወስዱ ሰዎች ቢያጋጥሙም አይደንቅም። ስለሆነም መምህራን
ከላይ በተመለከተው መሠረት በተግባር እንዲጠቀሙና እንዲያስተምሩ አደራ ተጥሎባቸዋል።
በኹለተኛ ደረጃ ትኵረት የሚሠጠው ጉዳይ በአማርኛ የፊደል ገበታ ላይ ሞክሼ ፊደላት የመኖራቸው ጉዳይ ነው። እዚህ ላይ የቆየውን
አተካሮ ትተን (ወደፊት መሠረታዊ እልባት እስኪያገኝ) በተቻለ መጠን በወጥነት ፊደላቱን መጠቀም ግን ለሌላ ጊዜ የሚተው
ባለመሆኑ በአሁኖቹ መጻሕፍት ውስጥ ትኵረት ለመስጠት ጥረት ተደርጓል። እንደመነሻ የተወሰደውም በአብዛኛው በጥቅም ላይ
እየዋሉ ያሉበት መንገድ ነው። በዚህም፣ ለምሳሌ ከመጻፍ ጋር የተገናኙትን ከነዝርዝራቸው ጽሕፈት፣ ጸሐፊ፣ መጻፍ፣ አጻጻፍ ወዘተ.፣
ከሥን ጋር የሚዋቀሩትን ሥነጽሑፍ፣ ሥነሕዝብ፣ ሥነሥርዓት ወዘተ.፣ ከሕግ ጋር የሚዋቀሩትን ሕገመንግሥት፣ ሕገተፈጥሮ፣
ሕገወጥ፣ ወዘተ፣ ዝርዝሩ ብዙ በመሆኑ ጉዳዩን በጥሞና በማጤንና መጻሕፍቱን በጥንቃቄ እያነበቡ፣ በመጻሕፍቱ ውስጥ በተጻፉበት
መንገድ መረዳትና በዚሁ ዓይነትም ለተማሪዎች ማስተማር ስለሚገባ መምህራን ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው።
በመጨረሻም መጠቀስ ያለበት ሌላው ከአጻጻፍ ጋር የሚያያዝ ጉዳይ የቋንቋ ክሂሎችን ለመሠየም የምንጠቀምበትና የምንጽፍበት
መንገድ ነው። ስለሆነም አራቱ የቋንቋ ክሂሎች በወጥነት ማዳመጥ (ማድመጥ አይደለም)፣ መናገር (ንግግር አይደለም)፣ ማንበብ
(ንባብ አይደለም) እና መጻፍ (ጽሕፈት ወይም ጽሑፍ አይደለም) በመሆናቸው በዚሁ ዓይነት መንገድ እንዲጻፉና በተግባር ላይ
እንዲውሉ ይጠበቃል።

xvi
ምዕራፍ አካባቢ ጥበቃ
1

የምዕራፉ ዓላማዎች

ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-


ƒƒ ያዳመጡትን ታሪክ መልዕክት ይናገራሉ፤
ƒƒ የክፍል ደረጃውን ታሪክ አንብበው ዝርዝር መረጃዎችን ይለያሉ፤
ƒƒ በአውድ ውስጥና ከአውድ ውጭ ለቃላት ፍቺ ይሰጣሉ፤
ƒƒ አያያዥ ቃላትን ተጠቅመው ድርብ ዓረፍተነገሮች ይፅፋሉ።

1.1.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) አካባቢያችን

አካባቢያችን

አካባቢ ሊበከል የሚችልባቸው መንገዶች ብዙ ናቸው። በየጊዜው የሚለቀቁ መርዛማና በካይ ጋዞች ለአካባቢ ብክለት ይዳርጋሉ።
ከፋብሪካዎች፣ ከመኪናዎች፣ ከወፍጮ ቤቶች ወዘተ የሚወጣው የተቃጠለ ጋዝ አካባቢን ይመርዛል። ቆሻሻን በአግባቡ
አለማስወገድ የአካባቢን ውበትና ጤናማነት ይቀንሳል። የደኖች መመንጠርም የአካባቢን ሚዛን በእጅጉ ያዛባል።

የአካባቢ መበከል ደግሞ ለበርካታ ችግሮች ይዳርጋል። አካባቢ ሲበከል የአየር ንብረት መዛባት፣ ጎርፍ፣ ድርቅና ረሃብ ይከሰታሉ።
ልዩ ልዩ አየርወለድና ውኃወለድ በሽታዎችም ይስፋፋሉ። የተፈጥሮ ሃብትም ይመናመናል። አፈር በጎርፍ ስለሚታጠብ መሬት
ለምነቷን ታጣለች፤ ምርታማነቷም ይቀንሳል። በአጠቃላይ የተበከለ አካባቢ ለኑሮ ምቹ አይሆንም። በዚህ የተነሳ ሰዎች ቀያቸውን
ለቀው ስለሚሰደዱ ለከፋ ስቃይ ይዳረጋሉ።
ëëë አካባቢን ከብክለት መጠበቅ የሚቻለው እንዴት ነው? ëëë

ይሁን እንጅ አካባቢን ከብክለት በመጠበቅ ለኑሮ ምቹ ማድረግ ይቻላል። ለዚህ ደግሞ በርካታ ርምጃዎችን መውሰድ ይጠይቃል።
ከመኖሪያ ቤቶችና ከድርጅቶች የሚወጣውን ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ በመለየት ሰብስቦ መቅበር ወይም እንደገና ወደምርት መቀየር
ተገቢ ነው። የተራቆተን መሬት በደን በመሸፈን የአፈር መሸርሸርን መከላከልና የአካባቢን ስነምህዳር መጠበቅ ያስፈልጋል። ወደህዋ
የሚለቀቀውን የተቃጠለ ጋዝ ለመቀነስ ታዳሽ የኃይል ምንጮችን በአማራጭነት መጠቀም ይገባል። እንዲህ ሲሆን አካባቢ ውብ፣
ለኑሮም ተስማሚ ይሆናል።

1 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 1


ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. ተማሪዎች በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ረጋ ብለው ኹለትጊዜ ያንብቡላቸው። ግምታቸውን እያረጋገጡ እንዲያዳምጡ ያድርጉ። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄው
ላይ ሲደርሱ ንባብዎን ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው። የተማሪዎችን ምላሽ ካዳመጡ በኋላ ንባቡን ይቀጥሉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንቃቄ ያዳምጣሉ፤]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስም ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በቃላቸው ይመልሳሉ። ግልጽ ያልሆነላቸውን ይጠይቃሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. ተማሪዎች ለቀረቡት ቃላት በታሪኩ መሠረት አውዳዊ ፍቺ እንዲጽፉ ይጠይቋቸው።ምሳሌ ሠርተው ያሳዩ።)
[ተ. ለተሰጡት ቃላት በትክክል አውዳዊ ፍቺ ይጽፋሉ።]
[የአካባቢ ሚዛን-ተፈጥሮ፣ መበከል- መመረዝ/ መቆሸሽ፣ ውኃወለድ- ውኃ አመጣሽ/ በውኃ የሚተላለፍ፣ ቀዬ- መንደር]

አቀላጥፎ ማንበብ (15 ደቂቃ)


(መ. “ጥንቸሏ” የሚለውን ታሪክ ከተማሪዎች ጋር በህብረት አቀላጥፋችሁ አንብቡ። ሁሉም ተማሪዎች ለማንበብ ዝግጁ መሆናቸውን
ያረጋግጡ። ከዚያም ከርስዎ ጋር በአንድነት አብረው እንዲያነቡ ያድርጉ። ይህ ዘዴ ለማንበብ የሚቸገሩ ተማሪዎች ካሉ
ሌሎቹን በማዳመጥ እየተከተሉ ማንበብን እንዲለማመዱ ዕድል የሚሰጥ ብልሃት ነው።)
[ተ. “ጥንቸሏ” የሚለውን ታሪክ ከመምህራቸው ጋር በህብረት አቀላጥፈው ያነባሉ።]

1.1.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ) ቁጭት

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. “ቁጭት” የሚለውን ታሪክ ከማንበባቸው በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ። ዐይነስውራን ተማሪዎች
ከጎናቸው ከሚገኙ ተማሪዎች ጋር እየተወያዩ እንዲሰሩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመ ንባብ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ታሪኩን እንዲያነቡ ያድርጉ፤እየተንቀሳቀሱ ማንበባቸውን ያረጋግጡ)
[ተ. ድምጽ ሳያሰሙ ታሪኩን በየግላቸው ያነባሉ።]

2 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 2


ድኅረንባብ (7 ደቂቃ)
(መ. ተማሪዎች ግለንባቡን አንብበው መጨረሳቸውን ካረጋገጡ በኋላ የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ
ያድርጉ፤የመጀመሪያውን ጥያቄ አርዓያ ሆነው ያሳዩአቸው።)
[ተ. የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. ከታሪኩ ለወጡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ይጠይቋቸው፤ በአዛምድ የቀረቡትንም ቃላት ከተመሳሳያቸው ጋር
እንዲያዛምዱ ያድርጉ፤ተማሪዎቹ ተግባራቱን ሠርተው ሲጨርሱ መልሳቸውን እጅ እያወጡ ለክፍሉ እንዲናገሩ ያድርጉ።)
[ተ. ለተሰጡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ፤ ቃላትን ከተመሳሳይ ፍቻቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

መጻፍ (13 ደቂቃ)


(መ. የቀረቡትን አያያዥ ቃላት በመጠቀም ድርብ ዓረፍተነገሮችን እንዲመሠርቱ ያድርጉ። ምሳሌ ሠርተው ያሳዩአቸው። ስለድርብ
ዓረፍተነገር የቀረበውን ማስታወሻ ተጠቅመው ማብራሪያ ይስጧቸው።)
[ተ. አያያዥ ቃላትን ተጠቅመው ድርብ ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

1.1.3 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) አካባቢያችን


(መ. “አካባቢያችን” በሚል ርዕስ ያነበቡላቸውን የማዳመጥ ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው። አንብበው ሲጨርሱ የድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎች ይጠይቋቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ይመልሳሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. ለተሰመረባቸው ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ፤የማስተካከያ መልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላት አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (15 ደቂቃ)


(መ. “ጥንቸሏ” የሚለውን ታሪክ አንድ አንድ አረፍተነገር እየተቀባበሉ በትክክል እንዲያነቡ ያድርጉ። እርስዎ አንድ አረፍተነገር
አንብበው ሲጨርሱ ሌላ ተማሪ ቀጣዩን አረፍተነገር እንዲያነብ በማድረግ ሂደቱን ያሳዩኣቸው።)
[ተ. ታሪኩን እየተቀባበሉ በትክክል ያነባሉ።]

1.1.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች በቃላት ዓረፍተነገር ሠርተው አውዳዊ ፍቻቸውን እንዲያሳዩ ይጠይቁ። ዓረፍተነገሮቹ አውዳዊ ፍቺ ማሳየታቸውን
ያረጋግጡ፤ ምሳሌ ይስጧቸው።)
[ተ. ቃላቱ አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]

3 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 3


መጻፍ (25 ደቂቃ)
(መ. የቀረበላቸውን ጅምር አንቀጽ አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ጅምሩን አንቀጽ አሟልተው ይጽፋሉ።]

1.1.5 ክለሳ (40 ደቂቃ) ታማኝ ጓደኛ

ቃላት (20 ደቂቃ)


1. (መ. ቃላትን ከተገቢ ቅጥያዎች ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ። ምሳሌ ይስጧቸው። አማራጭ መልሶችን መስጠት እንደሚችሉ
ያስታውሷቸው።)
[ተ. ዋናውን ቃል ከተገቢ ቅጥያዎች ጋር አጣምረው ይጽፋሉ።]
2. (ከታሪኩ ውስጥ ተስማሚ ቃላትን በመፈለግ ዓረፍተነገሮቹን እንዲያሟሉ ይጠይቁ።)
[ተ. ዓረፍተነገሮቹን ተስማሚ ቃላት ከታሪኩ በመፈለግ ያሟላሉ።]
ሀ. ነፍጓት ሐ. ያለስስት፣ ምድረበዳ ሠ. ለሞት
ለ. ምቾት መ. ረፍት]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. የተጀመረውን አንቀጽ ሐሳብ አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ጅምር አንቀጹን አሟልተው ይጽፋሉ።]

1.2.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) አስቴርና ሶፊያ

አስቴርና ሶፊያ

አስቴርና ሶፊያ ጓደኛሞች ናቸው። ሁለቱም የስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች ሲሆኑ በጣም ይዋደዳሉ። ሁለቱም ተመሳሳይ ባህርይ
አላቸው፤ ውይይት ይወዳሉ። ዘወትር በልዩልዩ ርዕሰጉዳዮች ላይ ይወያያሉ። ዛሬም በአንድ አሳሳቢ ጉዳይ ላይ ለመወያየት ቀጠሮ
ይዘዋል።
አስቴርና ሶፊያ በአካባቢያቸው በሚከሰቱ ችግሮች ላይ ተጨንቀዋል። የድርቅ ተደጋግሞ መከሰትም አሳስቧቸዋል። የትውልድ
ቀያቸው ሙቀት መጨመርም ረፍት ነስቷቸዋል። አካባቢያቸው በደራሽ ጎርፍ መሸርሸሩ ቆጭቷቸዋል። የምድር በረከት መቀነስም
አስደንግጧቸዋል። የዛሬው ውይይታቸው በዚህ ላይ ነው። የቀጠሮው ሰዓት ሲደርስ ተገናኙ።
ëëë
ለችግሮቹ ምን አይነት መፍትሔዎችን የሚጠቀሙ ይመስላችኋል? ëëë
በአካባቢያቸው የተከሰቱ ችግሮች በጣም እንዳሳሰቧቸው ተነጋገሩ። ለሙቀት መጨመርና ለድርቅ መከሰት ምክንያቶት በሆኑት
ጉዳዮች ላይ መወያየት ቀጠሉ። የችግሩ ዋነኛ ምንጭ የደኖች መመንጠር ስለመሆኑ ተስማሙ። ሰዎች ለማገዶ፣ ለቤት መስሪያና
ለአጥር ማጠሪያ ዛፎችን መቁረጣቸው ትክክል እንዳልሆነ ተግባቡ። ችግሩን ለማስወገድ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ማሰብ ጀመሩ።
ችግኞችን በብዛት መትከልና መንከባከብ ከተቻለ ችግሩ እንደሚቀረፍ ተማመኑ። ስለሆነም ራሳቸው አርዓያ ሆነው መታየት
እንዳለባቸው ተረዱ። በአካባቢያቸው ባለው ክፍት ቦታ ላይ አሥር አሥር ችግኞችን ሊተክሉ ተስማሙ። ጓደኞቻቸውንም
አስተባብረው በርካታ ችግኞችን ለመትከልና ለመንከባከብ ቃል ገቡ። ውይይታቸውን ሲጨርሱ የችግኝ መትከያ ጉዳጓድ ለመቆፈር
ተቀጣጥረው ተለያዩ።

4 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 4


ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከተማሪዎች ጋር ይወያዩ። ተማሪዎቹ የሚያስቡትን ይግለጹ እንጂ ማስተካከያ መስጠት
አያስፈልግም። ዓይነስውራን ተማሪዎች ካሉ በኹለተኛው ጥያቄ ላይ ያሳትፏቸው።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከመምህራቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. የሚከተለውን ታሪክ ረጋ ብለው ኹለት ጊዜ ያንብቡላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ጥያቄውን ይጠይቋቸው።
መልሳቸውን ከተቀበሉ በኋላ ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንደአስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በዓረፍተነገሮቹ ውስጥ ለተሰመረባቸው ቃላትና ሐረጋት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ይጠይቁ።)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላትና ሐረጋት አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)

ውሏችን ለአካባቢያችን
(መ. “ውሏችን ለአካባቢያችን” የሚለውን ምንባብ ከጓደኞቻቸው ጋር በመጋራት በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ማንበብን
ያለማምዱ። በዚህ ደረጃ ትኩረት የሚደረገው ምንባቡን አቀላጥፈው ማንበብ እንዲችሉ ማድረግ ላይ ነው። ስለሆነም
ምንባቡን ሲያነቡ በደንብ ተከታትለው ግብረ መልስ ይስጧቸው።)
[ተ. “ውሏችን ለአካባቢያችን” የሚለውን ታሪክ ከጓደኞቻቸው ጋር በመጋራት በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ማንበብን
ይለማመዳሉ።]

1.2.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ) ትጉህ አርሶአደሮች

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄ ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄ ላይ ከመምህር ጋር ይወያያሉ።]

5 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 5


የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)
(መ. ምንባቡን ለመረዳት በለሆሳስ እንዲያነቡ ያድርጉ። በዚህ ደረጃ ትኩረት የሚደረግበት አንብቦ መረዳት ነው።ስለሆነም ታሪኩን
በትክክል ማንበባቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል።)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው በለሆሳስ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል በመምረጥ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳአስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ትክክለኛ መልስ የያዘውን ሆሄ በመምረጥ ጥያቄዎቹን ይመልሳሉ።]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. በሳጥን ውስጥ ያሉትን ቃላት በተሰመረባቸው ቃላት ተክተው ዓረፍተነገሩን እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ። ቃላቱን በትክክል
መተካታቸውን ለማረጋገጥ መልሱን እንዲገልጹ ያድርጉ። እንደአስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. ቃላቱን በተመሳሳይ ቃላት ይተካሉ።]

መጻፍ (13 ደቂቃ)


(መ. ትጉህና ሰነፍ አርሶ አደርን በማወዳደር የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው እንዲጽፉ ይጠይቁ። ሐሳቦችን በመጨመር
ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. ትጉህና ሰነፍ አርሶአደሮችን አወዳድረው የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው ይጽፋሉ።]

1.2.3 ማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. “አስቴርና ሶፊያ” የሚለውን የማዳመጥ ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው። የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎች ያሰሯቸው።
እንደአስፈላጊነቱ የማስተካከያ መልስ ይንገሯቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ለቀረቡት ቃላት ይበልጥ የሚመሳሰላቸውን ቃል በመምረጥ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. ተመሳሳይ ቃላትን መርጠው ይመልሳሉ፤ 1.ለ 2.ሀ 3.ለ 4.ሀ 5.መ. 6.ሀ]

አቀላጥፎ ማንበብ (20 ደቂቃ)


(መ. “ውሏችን ለአካባቢያችን” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

6 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 6


1.2.4 መጻፍ

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ቃላቱን ከተመሳሳይ ፍቻቸው ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳይ ፍቻቸው ጋር ያዛምዳሉ። 1.መ 2.ሠ 3. ረ 4. ሀ 5. ለ]

መጻፍ (30 ደቂቃ)


(መ. የተጓደለውን አንቀጽ አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. የተጓደለውን አንቀጽ ተገቢ ቃላትንና ሐረጋትን በመጨመር አሟልተው ይጽፋሉ።]
መልስ
በትምህርትቤታችን ምንም አይነት ዛፍ አልነበረም። ፀሐይዋ ኃይለኛ ስትሆን ጥላ ስለሌለ ከክፍል ውጭ መቀመጥም ሆነ መቆም
አንችልም ነበር። ታዲያ አንድ ቀን የሳይንስ መምህራችን በአጥሩ ጥግ ጉድጓድ አስቆፈሩን። ከዚያም ሁላችንንም ወደችግኝ ጣቢያ
ይዘውን ሄደው ችግኝ አምጥተን እንድንተክል አደረጉ። ጧትና ማታ ተራ በተራ ካቅራቢያችን ወንዝ ውኃ በመቅዳት ችግኞቹን
እናጠጣቸው ነበር። ዛሬ ችግኞቹ አድገው ለማረፊያ ጥላ ለግቢያችንም ውበት ሆነዋል።

1.2.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ቅጥያዎቹን በተገቢ ቃላት ላይ እንዲጨምሩ ያድርጉ፣ እንደአስፈላጊነቱ የማስተካከያ ግብረ መልስ ይስጧቸው። አማራጭ
መልሶች ሊኖሩ እንደሚችሉ ልብ ይበሉ።)
[ተ. በቃላቱ ላይ ተስማሚ ቅጥያዎችን ይቀጥላሉ።]

መጻፍ (30 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎቹ በአካባቢያቸው ወይም በትምህርትቤታቸው በጋራ የሚሰሩ የልማት ስራዎችን በተመለከተ አንድ አጭር አንቀጽ
እንዲጽፉ ይጠይቋቸው። በቅድሚያ ኃይለቃል እንዴት መፃፍ እንዳለባቸው ያሳዩኣቸው፤ በመቀጠልም በዚያ ሐሳብ ሥር
የሚካተቱ ዝርዝር ሐሳቦችን እንዲያካትቱ ናሙና አንቀጽ ጽፈው ያሳዩኣቸው።)
[ተ. በአካባቢያቸው የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን በሚመለከት የተሟላ አንቀጽ ይጽፋሉ።]

7 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 7


1.3.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) ጣናን እንታደግ

ጣናን እንታደግ

ጣና ሀይቅ ልዩ በሆነ መልክዓምድራዊ ሂደት የተፈጠረ ነው። ተመራማሪዎች ከብዙ ዓመታት በፊት በተከሰተ የእሳተገሞራ ፍንዳታ
እንደተፈጠረ ያስረዳሉ።

ጣና ሀይቅ ከሰሜን እስከ ደቡብ 75 ኪ.ሜ. ይረዝማል። በተመሳሳይ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ያለው ርዝመት 60 ኪ.ሜ. ነው።
ጣና ሀይቅ 3600 ስኩየር ኪ.ሜ. ስፋት ይሸፍናል። ከባህር ወለል በላይ 1830 ሜትር ከፍታ አለው። ጣና በስፋቱ በኢትዮጵያ
አንደኛ ነው። በአፍሪካ ደግሞ ከቪክቶሪያና ከታንጋኒካ ሀይቆች ቀጥሎ የሶስተኛ ደረጃ ባለማዕረግ ነው። ከፍተኛው ጥልቀቱ 14
ሜትር ሲሆን አማካይ ጥልቀቱ ደግሞ 9 ሜትር ነው።

በሀይቁ ላይ የሚገኙት ጥንታዊ ገዳማትና ደሴቶች አለምአቀፍ የቱሪስት መስህብ በመሆን ያገለግላሉ። በትራንስፖርትና በዓሳ
ምርት አገልግሎት ስለሚሰጥ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው የጎላ ነው። ለአባይ ወንዝም ከፍተኛ የዉኃ መጠን ስለሚለግስ ለህዳሴው
ግድብ የወደፊት ተስፋ ነው።

ëëë የጣና ሐይቅ የዉኃ መጠን ቢቀንስ ወይም ቢበከል ምን ምን ጉዳቶች ሊከሰቱ ይችላሉ? ëëë

ይህ ለኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆን ለአለም ህዝብም ብርቅና ድንቅ፣ ሳቢና ማራኪ የሆነ ተፈጥሯዊ ሀብታችን በጠና ታሞ
በጣረሞት ላይ ይገኛል። ሀይቁ በዙሪያው በሚገኙ ነዋሪዎች በሚጣል ደረቅ ቆሻሻና በሚለቀቅ ፈሳሽ ቆሻሻ እየተመረዘ ነው።
“እምቦጭ” በሚባል አደገኛ መጤ አረም ሰፊው የሀይቁ አካል እየተወረረ ነው። ከከፍተኛ ቦታዎችና ባካባቢው ከሚገኙ የእርሻ
መሬቶች በጎርፍ እየተሸረሸረ በሚገባው ደለል የውኃ መጠኑ በእጅጉ እየቀነሰ ነው። በሀይቁ ላይ የተጋረጠውን ከፍተኛ አደጋ
ድንበር ሳንለይ በአገርአቀፍ ደረጃ ስልት ዘይደንና በጀት መድበን መታደግ ይኖርብናል። በመሆኑም “ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ
መጠንቀቅ” ነውና ሁላችንም በመረባረብ ጣናን እንታደግ።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ። ለቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ግብረመልስ መስጠት አያስፈልግም።
ራሳቸው ታሪኩን አዳምጠው ግምታቸው ትክክል ወይም ስህተት መሆኑን ያረጋግጣሉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከመምህር ጋር ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. የሚከተለውን ታሪክ ኹለት ጊዜ ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። በመቀጠልም ንባብዎን ገታ አድርገው የማዳመጥ ሂደት ጥያቄውን
ይጠይቋቸው። ከዚያም ማንበብዎን ይቀጥሉ!)
[ተ. ምንባቡን መምህር ሲያነቡ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ፤ ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን አንብበው ሲጨርሱ የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎችን ይጠይቋቸው።)
[ተ. የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ፤ ግልጽ ያልሆነላቸውን ይጠይቃሉ።]

8 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 8


ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. ምንባቡን መሠረት አድርገው ለቀረቡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ።)
[ተ. - ደሴት - በውኃ የተከበበ ደረቅ ቦታ]
- መስህብ - ቱሪስት የሚጎበኘው ሳቢ ቅርስ/ የቱሪስት መዳረሻ]
- መዘየድ - ብልሃት መፈለግ]

አቀላጥፎ ማንበብ (15 ደቂቃ)


መ. (“ስንዱና ማንጎዎቹ” የሚለውን ምንባብ ከጓደኞቻቸው ጋር እየተጋሩ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ
ያድርጉ። በዚህ ደረጃ ትኩረት የሚደረግበት ተማሪዎች አቀላጥፈው ማንበብ መቻላቸው ነው። ሲያነቡ በመከታተል
እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ በመስጠት ያግዟቸው። አርዓያ ሆነውም ያሳዩአቸው።)
[ተ. “ስንዱና ማንጎዎቿ” የሚለውን ምንባብ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

1.3.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. ተማሪዎች ምንባቡን ከማንበባቸው በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጓቸው።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎቹ “ሳይቃጠል በቅጠል” የሚለውን ታሪክ ለመገንዘብ በጥልቀት እንዲያነቡ ያድርጉ። የማንበብ ሂደታቸውን
በመከታተል እንዳስፈላጊነቱ ድጋፍ ያድርጉላቸው።)
[ተ. ምንባቡን በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ እየተገነዘቡ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድረጉ። እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ መልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ፤ መልሳቸውን ለመምህር ይገልጻሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. የቀረቡትን ቃላት በምንባቡ መሠረት ከተመሳሳይ ፍቻቸው ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ። ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳይ ፍቻቸው ጋር ያዛምዳሉ። የሠሩትን ለመምህር ያቀርባሉ።]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. የቀረቡትን ሐሳቦች “የደን ጠቀሜታ” ና “የደን መጨፍጨፍ ጉዳት” በሚሉት ርዕሶች ሥር እንዲመድቡ ያድርጉ።)
[ተ. ዝርዝር ሐሳቦቹን በተሰጡት ርዕሶች ሥር ይመድባሉ።]

9 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 9


1.3.3 ማዳመጥ (20 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. “ጣናን እንታደግ” የሚለውን ምንባብ ደግመው ያንብቡላቸው። ተማሪዎች ታሪኩን እንዲከታተሉ ያድርጉ።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ደግመው ሲነያቡ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንደአስፈላጊነቱ መልስ ይንገሯቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ፤ መልሳቸውን ለመምህር ያቀርባሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በቀረቡት ቃላት ዓረፍተነገር በመስራት አውዳዊ ፍቻቸውን እንዲያሳዩ ያድርጉ። ትክክለኛ አውድ የሚያሳይ ዓረፍተነገር
መስራታቸውን ይከታተሉ። ምሳሌ ሊሰጧቸው ይችላሉ።)
[ተ. ቃላቱ አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]
መልስ፡- ኩራታችን የሆነው የጣና ሐይቅ በደረሰበት ችግር በጠና ታሟል። ክፉኛ፣ በአስከፊ ሁኔታ። ይህን ትርጉም ያስገኘው አውድ
በደረሰበት ችግር እና ታሟል የሚለው ነው።

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ስንዱና ማንጎዎቹ” የሚለውን ታሪክ ከጓደኞቻቸው ጋር እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ
ያድርጉ። ሁሉም ተማሪዎች ታሪኩን አቀላጥፈው እንዲያነቡ ድጋፍ ያድርጉላቸው። እንዳስፈላጊነቱ ግብረ መልስ ይስጧቸው።)
[ተ. “ስንዱና ማንጎዎቹ” የሚለውን ታሪክ በጥንድ በእየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

1.3.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. በዓረፍተነገሩ ውስጥ የተሰመረባቸውን ቃላት ከታሪኩ እየፈለጉ በተመሳሳይ ቃላት እንዲተኩ ያድርጉ።)
[ተ. በዓረፍተነገሮቹ የተሰመረባቸውን ቃላት ሌሎች ቃላትን ከታሪኩ በመፈለግ ይተካሉ።]
መልስ [ተ. ድሎት - ምቾት ጋሻ - - መከታ]
ፈታ - - ዘና ያስደስታታል - - ያረካታል]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. በሳጥን ውስጥ የቀረቡትን ሥርዓተ ነጥቦች በዓረፍተነገሮች ውስጥ በተገቢ ቦታቸው ተጠቅመው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ ማስተካከያ
ይስጧቸው። የሥርዓተነጥቦችን አገልግሎት በተመለከተ በታችኞቹ የክፍል ደረጃዎች የተማሯቸውን ያስታውሷቸው። ድርብ
ሰረዝ (፤) የሐሳብ ተዛምዶ ባላቸው ተከታታይ ዓረፍተነገሮች መካከል ይገባል። ትዕምርተ አንክሮ/ቃልአጋኖ (!) በስሜት
ከተነገሩ ቃላት፣ ሐረጋትና ዓረፍተነገሮች በኋላ ይገባል።)
[ተ. ሥርዓተነጥችን በተገቢ ቦታቻው በማስገባት ዓረፍተነገሮቹን እንደገና ይጽፋሉ።]

10 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 0


1.3.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. በቃላቱ ውስጥ ያሉትን ቅጥያዎች ለይተው እንዲጽፉ ይጠይቋቸው።
[ተ. ከቃላቱ ላይ ቅጥያዎችን ነጣጥለው ይጽፋሉ።]
[ተ. ማንጎዎች = ማንጎ -ዎች
ደጋማ = ደጋ -ኣማ
ሰልፈኛ = ሰልፍ -ኧኛ
ልባም = ልብ -ኣም]

መ.(ለቀረቡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ይጠይቋቸው። ማስተካካያ ይጻፉላቸው።)


[ተ. ለቃላቱ አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ። መልሳቸውን ለመምህር ያቀርባሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች ፍሬያቸው የሚበላ ተክሎችን ጠቅሰው ምን ምን ጠቀሜታ እንደሚሰጡ አጭር አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ። የሐሳብ
አደረጃጀታቸውን በተመለከተ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ፍሬያቸው የሚበላ ተክሎችን በመጥቀስ ስለጠቀሜታቸው አጭር አንቀጽ ይጽፋሉ።]

11 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አካባቢ ጥበቃ 01


ምዕራፍ የመንገድ ደህንነት
2

የምዕራፉ ዓላማዎች

ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-


ƒƒ የመንገድ ደህንነት መዝሙሮችን ካዳመጡ በኋላ ይዘምራሉ፤
ƒƒ የአቀላጥፎ ማንበብ ባህርያትን በመላበስ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው አጭር አንቀፅ ያነባሉ፤
ƒƒ ቃላትን ከእውናዊ ህይወት ጋር ያዛምዳሉ፤
ƒƒ አያያዥ ቃላትን በመጠቀም ድርብ ዓረፍተነገሮችን ይፅፋሉ።

2.1.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) የትምህርትቤታችን እንግዳ

የትምህርትቤታችን እንግዳ

ዛሬ በትምህርትቤታችን ውስጥ አንድ እንግዳ ተገኝተዋል። የኢትዮጵያን ብሄራዊ መዝሙር ዘምረን ሰንደቅዓላማችንን ሰቅለናል።
ርዕሰመምህሯ ከእንግዳው ጋር ሊያስተዋውቁን ንግግራቸውን ጀመሩ። “እንደምን አደራችሁ ተማሪዎች? በመካከላችን የተገኙት
እንግዳ ከመንገድ ትራንስፖርት መስሪያቤት የመጡ ናቸው። አጭር ትምህርት ስለሚሰጧችሁ በጽሞና ተከታተሉ” አሉን።

እንግዳውም ርዕሰመምህራችንን አመስግነው ንግግራቸውን ቀጠሉ። “እንደምን አደራችሁ ተማሪዎች?” አሉና ምላሻችንን
ሳይጠብቁ ወደትምህርቱ አመሩ። “ስለመንገድ ላይ ደህንነት ለማስተማር ነው የመጣሁት። በአገራችን ብሎም በክልላችን
በየጊዜው በርካታ ሰዎች በመኪና አደጋ ጉዳት ይደርስባቸዋል። ስለሆነም ራሳችሁን ከአደጋ ልትጠብቁ ይገባል። በመኪና መንገድ
ላይ መጫወት ራስን ለጉዳት ያጋልጣል። ምንጊዜም የእግረኛ መንገድ ብቻ ተጠቀሙ። ግራ አቅጣጫችሁን ይዛችሁ መጓዝንም
አትርሱ። ምክንያቱም መኪና ሲመጣ ፊትለፊት የማየት እድል ይፈጥርላችኋል” አሉና ወደያዙት ማስታወሻቸው አቀረቀሩ።

ëëë
እስካሁን ካዳመጣችሁት ታሪክ ምን ተረዳችሁ?ëëë

አሁንም ንግግራቸውን ቀጠሉ። “መንገድ ማቋረጥ ስትፈልጉ ደግሞ የእግረኛ ማቋረጫዎችን ተጠቀሙ። በዚህ ጊዜም ቢሆን
መኪና ወይም ሌሎች ተሸከርካሪዎች አለመምጣታቸውን ማረጋገጥ ይኖርባችኋል። ተምራችሁ ለአገራችሁ፣ ለማኅበረሰባችሁና
ለወላጆቻችሁ ልትጠቅሙ የምትችሉት ራሳችሁን ከአደጋ ስትጠብቁ ብቻ ነው” ካሉ በኋላ ሰዓታቸውን ተመለከቱ። በመጨረሻም
ወደርዕሰመምህሯ ዞረው ምስጋና በማቅረብ ትምህርታቸውን አጠናቀቁ።

12 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት 02


ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. ተማሪዎች በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ። ማንኛውንም የሚታሰባቸውን መልስ እንዲናገሩ ያበረታቱ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. የሚከተለውን ምንባብ ረጋ ብለው ኹለት ጊዜ ያንብቡላቸው። ተማሪዎች በንቃት ማዳመጣቸውን ይከታተሉ። የማዳመጥ
ሂደት ጥያቄው ላይ ሲደርሱ ንባብዎን ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ከዚያም ንባቡን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህር የሚያነቡላቸውን ምንባብ ማስታወሻ እየያዙ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። ሠርተው ሲጨርሱ ለክፍሉ ያቅርቡ። እንዳስፈላጊነቱ
ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ። መልሳቸውን ለመምህር ያቀርባሉ።]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ.ዓረፍተነገር በመስራት የቃላቱን አውዳዊ ፍቺ እንዲያሳዩ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ምሳሌ ይስጡ።)
[ተ. የቃላቱን አውዳዊ ፍቺ በዓረፍተነገር ያሳያሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (13 ደቂቃ)


(መ. “ምርትነሽ” የሚለውን ታሪክ ርስበርስ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ በማድረግ አቀላጥፎ
ማንበብን እንዲለማመዱ ያድርጉ። ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች ድጋፍ ይስጡ።)
[ተ. “ምርትነሽ” የሚለውን ታሪክ ርስበርስ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

2.1.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ውይይት እንዲያካሂዱ ይጠይቁ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ያደርጋሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች ታሪኩን በአስተውሎት እንዲያነቡ ያድርጉ። ሁሉም ተማሪዎች ማንበባቸውን ያረጋግጡ።)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው በትኩረት ያነባሉ፤ ይረዳሉ።]

13 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት 03


ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጡ።)
[ተ. ምንባቡን አንብበው ሲጨርሱ የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. ተማሪዎች ቃላቱን ከተቃራኒያቸው ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ። በትክክል ማዛመዳቸውን ያረጋግጡ፤ እንዳስፈላጊነቱ
ማስተካከያ ይስጡ።)
[ተ. የተሰጡትን ቃላት ከተቃራኒያቸው ጋር ያዛምዳሉ። መልስ 1. ሐ 2. ሠ 3. ረ 4. ሰ 5. ለ]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች የተጀመረውን ታሪክ አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ። የጻፉትን ታሪክ እንዲያነቡ ይርዷቸው።)
[ተ. ጅምሩን አንቀጽ አሟልተው ይጽፋሉ። አንቀጹን እንደሚከተለው አሟልቶ መጻፍ ይቻላል።]
አንድ ዓይነስውር ሰው መኪና ከበዛበት መንገድ ዳር ቆሟል። መንገዱን በማቋረጫው ለመሻገር በጣም ተቸግሯል። ከቆመ ረጅም
ሰዓት ሆኖታል። አንዲት ተማሪ ወደትምህርት ስትሄድ እንደተቸገረ ከሁኔታው ተገነዘበች። አጠገቡ ሄዳ እጁን ያዘችው። ለመኪናዎች
ቀይ መብራት እስኪበራ ጠበቀች። መብራቱ በራ፤ ሁሉም መኪናዎች ቆሙ። ከዚያም ግራ ቀኟን አየችና በመንገዱ ማቋረጫ ላይ
ይዛው ተሻገረች። የሚሄድበትን አቅጣጫ አስያዘችውና ወደትምህርትቤቷ ሄደች። ሰውዬውም አመስግኗት ሄደ።

2.1.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)


(መ. የትምህርትቤታችን እንግዳ የሚለውን ምንባብ በድጋሚ ያንብቡላቸው። በመቀጠል የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ
እንዲሰሩ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጡ።)
[ተ. ምንባቡን ደግመው በማዳመጥ የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይሠራሉ።]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. በዓረፍተነገሮቹ ውስጥ የተሰመረባቸውን ቃላት በሳጥን ውስጥ ካሉት መርጠው እንዲተኩ ያድርጉ። መልሳቸው ትክክል
መሆኑን በማረም ያረጋግጡ።)
[ተ. በዓረፍተነገሮቹ ውስጥ የተሰመረባቸውን ቃላት በተመሳሳይ ቃላት ይተካሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (18 ደቂቃ)


(መ. “ምርትነሽ” በሚል ርዕስ የቀረበውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክልና በፍጥነት እንዲያነቡ ያድርጉ። አንድ አንቀጽ
አቀላጥፎ በማንበብ አርዓያ ሆነው ያሳዩ። የተወሰኑ ተማሪዎች ታሪኩን ጮክ ብለው እንዲያነቡ በማድረግ እንዳስፈላጊነቱ
ማስተካካለያ ይስጡ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክልና በፍጥነት ያነባሉ።]

14 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት 04


2.1.4 መጻፍ (40 ደቂቃ) ታማኝ ጓደኛ

ቃላት (20 ደቂቃ)


(መ. ከታሪኩ ውስጥ ተስማሚ ቃል እየፈለጉ ዓረፍተነገሮቹን እንዲያሟሉ ያድርጉ።)
[ተ. ከታሪኩ ውስጥ ተስማሚ ቃል እየፈለጉ ዓረፍተነገሮቹን አሟልተው ይጽፋሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች ታሪኩን መሠረት አድርገው የሐሳብ ማዳራጃ ቢጋሩን እንዲያሟሉ ያድርጉ ። እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ
ይስጧቸው።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በታሪኩ መሠረት ያሟላሉ።]
[ተ. የእግረኛ መስመር ብቻ መጠቀም፣ ግራ አቅጣጫን ይዞ መጓዝ፣ በዜብራ መስመር ብቻ ማቋረጥ]

2.1.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. ለቃላቱ ተስማሚ ቅጥያዎችን እየመረጡ እንዲቀጥሉ ያድርጉ። ቅጥያዎቹን በትክክል መስራታቸውን ለማረጋገጥ ግብረመልስ
ይስጧቸው።)
[ተ. ቃላቱንና ቅጥያዎቹን አስማምተው ይጽፋሉ። መልስ እግረኛ፣ መሻገሪያ፣ ህልመኛ፣ ጤናማ]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ ውስጥ ሐሳቦችን ጽፈው እንዲያሟሉ ያድርጉ። ትክክል መሆናቸውን ያረጋግጡ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በተፈላጊ ሐሳቦች አሟልተው ይጽፋሉ።]

2.2.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) የትራፊክ ፖሊስ

የትራፊክ ፖሊስ

የትራፊክ ፖሊስ የመንገድ ላይ ደንቦችን የሚያስከብር ባለሙያ ነው። በመኪና አደጋ ምክንያት የሰው ህይወትና ንብረት ጉዳት
እንዳይደርስበት የሚቆጣጠርና ህግን የሚያስከብር ሰው ነው። ሹፌሮች ጠጥተው እንዳያሽከረክሩ፣ በፍጥነት እንዳይነዱና ዕቃና ሰው
ከልክ በላይ እንዳይጭኑ ይቆጣጠራል።

በተለይ በትልልቅ ከተሞች ተሽከርካሪዎች መስቀለኛ መንገድ ላይ ተራቸውን ጠብቀው እንዲተላለፉ የሚያደርጉት አረንጓዴ፣ ቢጫና
ቀይ መብራቶች በትክክል መስራታቸውን ይከታተላል። ሰዎች ለማቋረጫ ተብሎ በተዘጋጀ የዜብራ መስመር ብቻ ተጠንቅቀውና
ተራቸውን ጠብቀው እንዲተላለፉ ያስተምራል።

15 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት 05


ëëë አሽከርካሪዎች የሚቆሙት የትኛው መብራት ሲበራ ነው? ëëë

ማንኛውም አሽከርካሪ ቀይ መብራት ሲበራ መቆም ይኖርበታል። ቢጫ ሲበራ መዘጋጀትና አረንጓዴ ሲበራ ማለፍ እንዳለበት ሊያውቅ
ይገባዋል። የመብራት ደንብ አክብሮ፣ ተራውን ጠብቆ የማያሽከረክር ሹፌር ለአደጋ ተጋላጭ ይሆናል። በተለይ በመስቀለኛ መንገዶች
አሽከርካሪዎች ያለተራቸው ለማለፍ ሲሽቀዳደሙ ለአደጋ ይዳረጋሉ። በዚህ መልኩ በሀገራችን በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰው
አደጋ የትየለሌ ሆኗል።

ስለሆነም የትራፊክ ፖሊስ የመኪና አደጋዎችን ለመቀነስና ለመከላከል ተግቶ የሚሰራ ነው። ከቅርብ አመታት ወዲህ አደጋዎችን
ለመቀነስ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችንም እያሳተፈ ይገኛል። በትምህርትቤትና በቀበሌ ፈቃደኛ ወጣቶችን በመመልመል የመንገድ
ላይ ደህንነት ስልጠና እየሰጠ ነው። ወጣቶች ከስልጠና በኋላ በተመረጡ የመኪና መንገዶች የትራፊክ ደንቦችን እንዲያስከብሩ
አሰማርቷል። የትራፊክ ፖሊስ በእግረኞች ስህተት፣ በሹፌሮች ችኩልነትና በመኪና ብልሽት ምክንያት አደጋ እንዳይከሰት ጥረት
ያደርጋል። በዚህም የሰው ልጆችን ህይወት ከሞት፣ ንብረታቸውንም ከጥፋት ለመታደግ የሚሰራ ትጉህ ባለሙያ ነው ሊባል ይችላል።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከተማሪዎች ጋር ይወያዩ። ዐይነስውራን ተማሪዎች ካሉ በኹለተኛው ጥያቄ ላይ ሐሳባቸውን
እንዲናገሩ ይጠይቋቸው።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “የትራፊክ ፖሊስ” የሚለውን ታሪክ እንዲረዱት ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። እንዳስፈላጊነቱ ደግመው ሊያነቡላቸው ይችላሉ።
የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ማንበብዎን ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው።)
[ተ. ታሪኩን መምህር ሲያነቡ ያዳምጣሉ፤ ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. በመቀጠል የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን እንዲያሟሉ ያድርጉ። ምሳሌ ሠርተው ያሳዩአቸው።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በተፈላጊ ሐሳቦች አሟልተው ይጽፋሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (15 ደቂቃ)


(መ. “ጊዜሽና አባቷ” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክልና በፍጥነት እንዲያነቡ ያድርጉ።
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክልና በፍጥነት ያነባሉ።]

16 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት 06


2.2.2 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ) እኔ ማነኝ

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. “እኔ ማነኝ?” የሚለውን ታሪክ ከማንበባቸው በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (5 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን በየግላቸው እንዲያነቡ መመሪያ ይስጧቸው። ማንበባቸውን እየተንቀሳቀሱ ይከታተሉ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (7 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። መልሳቸውን ለክፍሉ እንዲያቀርቡ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ
ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. ቃላት በታሪኩ ውስጥ ባላቸው አውዳዊ ፍቺ ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጉ። የሠሩትን ያርሙላቸው።)
[ተ. ቃላቱ በታሪኩ ውስጥ ባላቸው አውዳዊ ፍቺ ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]

መጻፍ (18 ደቂቃ)


(መ. “መምህር፣ አርሶአደር ፣ ወታደር” ከሚሉት ሙያዎች መካከል አንዱን በመምረጥ እኔ ማነኝ? የሚል አንድ አንቀጽ እንዲጽፉ
ያድርጉ። የጻፉትን አንቀጽ ይገምግሙላቸው። እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ ሊሰጡበት ይችላሉ።)
[ተ. ከተሰጡት ርዕሶች አንዱን መርጠው “እኔ ማነኝ?” በሚል ርዕስ አንቀጽ ይጽፋሉ።]
ምሳሌ [ተ. የዘወትር ምኞቴ ልጆችን በዕውቀትና በጥሩ ስነምግባር ኮትኩቼ ለቁምነገር ማብቃት ነው። ሁልጊዜ አነባለሁ፤ ከእጄ ላይ
መጻህፍት ተለይተው አያውቁም። የምጠቀምባቸውን ቁሳቁሶች አሟልቼና በደንብ ተዘጋጅቼ ክፍል ውስጥ እገባለሁ። ትምህርት
የጠማቸውንና የዕውቀት ብርሃንን የሚፈልጉ ተማሪዎቼን ዐይን ሳይ በጣም ደስ ይለኛል። ተማሪዎቼ ትልቅ ደረጃ ደርሰው ራሳቸውን፣
ቤተሰባቸውንና ሀገራቸውን እንዲጠቅሙ ሌት ከቀን እሰራለሁ። እኔ ማነኝ?]

2.2.3 ማዳመጥ (10 ደቂቃ)

ድኅረማዳመጥ
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን እውነት ወይም ሀሰት በማለት እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን እውነት ወይም ሐሳብ በማለት ይመልሳሉ።]

17 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት 07


ቃላት (15 ደቂቃ)
መ. (ለተሰመረባቸው ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ። ተማሪዎቹ መልሳቸውን ካቀረቡ በኋላ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. መስቀለኛ- መገናኛ፣ ብልሽት-ችግር፣ የትየለሌ-በርካታ]

አቀላጥፎ ማንበብ (15 ደቂቃ)


መ. (“ጊዜሽና አባቷ” የሚለውን ምንባብ በቡድን እየተራረሙ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ።
አቀላጥፈው ማንበባቸውን ያረጋግጡ። አንድ አንቀጽ አቀላጥፈው በማንበብ አርአያ ሆነው ያሳዩ።)
[ተ. ታሪኩን በቡድን ሆነው እየተራረሙ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

2.2.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. አያያዥ ቃላቱን ተጠቅመው ዓረፍተነገሮቹን እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ። የሰሯቸውን ዓረፍተነገሮች ያርሙ። አስፈላጊ ከሆነ
ማስተካከያ ይስጧቸው)
[ተ. አያያዥ ቃላት ተጠቅመው ዓረፍተነገሮቹን ይጽፋሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. መንገድ ሲያቋርጡ የሚከተሏቸውን ህጎች በቅደምተከተል እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ . “ዜብራ መስመር ብቻ ለመጠቀም መወሰን፣ አረንጓዴ መብራት እስኪበራ መጠበቅ፣ ግራና ቀኝ መመልከት፣ ፈጥኖ ማለፍ/
መሻገር “ ብለው ይጽፋሉ።]

2.2.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (20 ደቂቃ)


(መ. በቃላቱ ላይ ያሉትን ቅጥያዎች ነጥለው እንዲያወጡ ያድርጉ። ቅጥያዎቹን በትክክል ማውጣታቸውን ያረጋግጡ። በዚህ ደረጃ
ስለእያንዳንዱ ቅጥያ ምንነትና ተግባር ማብራሪያ መስጠት ተገቢ አይደለም።)
[ተ. ቃላቱንና ቅጥያዎቹን ነጣጥለው ይጽፋሉ።]
(መ. የቀረቡት ቃላት ኹለት ትርጉም የሚሰጡ ናቸው። ተማሪዎቹ ዓረፍተነገር በመስራት ኹለት ትርጉም ሠርተው እንዲያቀርቡ
ያድርጉ። ከመጀመሪያው ቃል ውጭ ያሉት ቃላት በማጥበቅና በማላላት ሲነበቡ ኹለት ፍቺ ሊሰጡ እንደሚችሉ ሊጠቁሟቸው
ይችላሉ።ማስተካከያም ይስጧቸው።)
[ተ. በቃላቱ ኹለት ኹለት ዓረፍተነገር በመስራት የተለያየ ፍቺ እንዳላቸው ያሳያሉ።]

18 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት 08


መጻፍ (20 ደቂቃ)
መ. (አያያዥ ቃላቱን ተጠቅመው አንቀጹን እንዲያሟሉ ያድርጉ። የጻፉትን አንቀጽ ያስነብቧቸው።)
[ተ. አያያዥ ቃላቱን ተጠቅመው አንቀጹን ያሟላሉ።]

2.3.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) ፍጥነትና መዘዙ

ፍጥነትና መዘዙ

ይደርሳል ተስፋ ይባላል። ከአባቱ ከአቶ ተስፋ አለኸኝና ከእናቱ ከወ/ሮ ስመኝ ቀራለም ሰኔ 19 ቀን 1972 ዓ.ም. በባህርዳር ከተማ
ተወለደ። እናትና አባቱ ፈጣሪ ሀብት የሰጣቸው ስለሆኑ ተቀማጥሎ ያደገ መልከመልካም፣ ቁመቱ ሎጋ፣ ሲያዩት የሚያማልል ልጅ
ነበር።

እድሜው ለትምህርት ሲደርስ በሰርፀድንግል አንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት ትምህርቱን መከታተል ጀመረ። ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ
ጎበዝ ተማሪ ሰለነበር በ1990 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍልን በከፍተኛ ውጤት አጠናቀቀ። በ1991 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
የህክምና ትምህርቱን ለሰባት ዓመታት ተከታትሎ በ1997 ዓ.ም በማዕረግ ተመረቀ።

እናትና አባቱ፣ እህትና ወንድሙ እንደማለዳ ፀሐይ ፈክተውና ባላቸው ልብስና ጌጥ አሸብርቀው ሊያስመርቁት ወደ አዲስ አበባ
ሄዱ። እዚያው አዲስ አበባ የሚኖሩ ዘመዶቻቸውን ጨምሮ በአንድ ሆቴል ውስጥ ሲበሉና ሲጠጡ ፣ ሲዘፍኑና ሲጨፍሩ አመሹ።
እኩለ ሌሊት ሲሆን ድካም ተሰማቸውና ወደየአልጋ ክፍላቸው ሄደው ከነልብሳቸው ተጋደሙ፤ ወዲያው እንቅልፍ ጣላቸው።

ወደባህርዳር ለመመለስ ማልደው ተነሱ። በመጠጥ ብዛት የተነሳ ድካም እያናወዛቸው ሁሉም አንድ ላይ በግል መኪናቸው
ተሳፈሩ። የመኪናዋን መሪ የጨበጡት የቤተሰቡ አባወራ ናቸው። አባወራው ከፍ ባለ ድምጽ ባህላዊ ዘፈን ከፍተዋል። የቤተሰቡ
አባላት ድካም ቢሰማቸውም ከሙዚቃው ጋር ማዜም ጀምረዋል። አባወራው አንዳች በሆነ የደስታ ስሜት ውስጥ ሆነው መኪናዋን
እንደአውሎ ነፋስ ያከንፏት ጀመር።

ëëë በቀጣይ ምን የሚፈጠር ይመስላችኋል? ëëë

ተመራቂውና አስመራቂው ቤተሰብ በሙሉ በአንድነት “አባዬ! ቀስ በል! አባዬ! ቀስ በል!” እያሉ ይጮሀሉ። የሰማቸው ግን
አልነበረም። ከአዲስ አበባ ከንጋቱ በአስራአንድ ሰዓት የተነሳችው መኪና ጠመዝማዛውን መንገድ ተያይዘዋለች። ደስታ ያሰከራቸው
አባት ፍጥነታቸውን ጨምረዋል። ቤተሰቦቻቸው ቢማፀኗቸውም ሊሰሟቸው ፈቃደኛ አልሆኑም።

“ሞት የጠራውን ገላጋይ አያስቀረውም” እንደተባለው ወደድልድዩ መታጠፊያ ሲደርሱ መኪናዋ መንገዱን ስታ ቁልቁል
ወደሸለቆው በአየር ላይ ተንሳፈፈች።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. “ፍጥነትና መዘዙ” የሚለውን ታሪክ ከማዳመጣቸው በፊት በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ይወያያሉ።]

19 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት 09


የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)
(መ. ተማሪዎችን ለማዳመጥ ያዘጋጁ። ምንባቡን ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ምንባቡን ገታ
አድርገው ይጠይቋቸው። ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህሩ የሚያነቡላቸውን ታሪክ በጥሞና ያዳምጣሉ። ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ የማስተካከያ መልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. የተሰመረባቸውን ቃላት ከተሰጡት ቃላት ውስጥ በመምረጥ እንዲተኩ ያድርጉ።)
[ተ. የተሰመረባቸውን ቃላት በሌላ ቃል ይተካሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “የትራፊክ መብራት” የሚለውን ታሪክ በህብረት እንዲያነቡ ያድርጉ። የፊደል ግድፈት፣ የድምጽ አወጣጥ፣ ሥርዓተነጥቦችን
ወዘተ በሚመለከት ማስተካከያ ይስጧቸው። በህብረት ንባቡ አብረው በማንበብ ያግዟቸው።)
[ተ. ታሪኩን በህብረት ያነባሉ።]

2.3.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ) የሰፈሬ ልጆች

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
መ. (የሰፈሬ ልጆች የሚለውን ታሪክ ከማንበባቸው በፊት በጥያቄዎቹ ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ። መልስ መስጠት
አያስፈልግም።)
[ተ. በቅድመ ማንበብ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


መ. (“የሰፈሬ ልጆች” የሚለውን ምንባብ በለሆሳስ እየተገነዘቡ እንዲያነቡ ያድርጓቸው። ሁሉም ተማሪዎች በአስተውሎት እያነበቡ
ስለመሆናቸው ያረጋግጡ።)
[ተ. ምንባቡን ለመረዳት ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

20 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት !


ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. ተመሳሳይ ቃላትን በማዛመድ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳይ ፍቻቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

መጻፍ (13 ደቂቃ)


(መ. የተጓደለውን አንቀጽ በተገቢ ሐሳብ አሟልተው እንዲጽፉ መመሪያ ይስጧቸው።)
[ተ. የተጓደለውን አንቀጽ አሟልተው ይጽፋሉ።]

2.3.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎቹ ለማዳመጥ ዝግጁ መሆናቸውን ካረጋገጡ በኋላ ታሪኩን ደግመው ያንብቡላቸው። በመቀጠል የድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎችን በቃላቸው እንዲሰሩ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በቃላቸው ይሠራሉ።]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. በቀረቡት ቃላት በታሪኩ መሠረት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ በማድረግ ዓረፍተነገር እንዲሰሩ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ
ለመልሳቸው ማስተካካያ ይስጧቸው።)
[ተ. ቃላቱ በታሪኩ መሠረት አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር ይሠራሉ። መልስ፡- ጎብኚዎቹ ወደጎንደር ለመሄድ
በየመኪናቸው ተሳፈሩ። (ገቡ ለማለት)]

አቀላጥፎ ማንበብ (18 ደቂቃ)


(መ. የትራፊክ መብራት የሚለውን ምንባብ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጓቸው።
አንድ አንቀጽ በማንበብ አርዓያ ሆነው ያሳዩ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ምንባቡን ጥንድ ጥንድ ሆነው እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

2.3.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (20 ደቂቃ)


(መ. የቀረቡትን ቃላት ከታሪኩ ውጪ ያላቸውን ፍቺ በዓረፍተነገር እንዲያሳዩ ያድርጉ። እንደአስፈላጊነቱ ምሳሌ ይስጧቸው።)
[ተ. ቃላቱ ከአውዱ ውጪ ባላቸው ፍቺ ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]

21 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት !1


መጻፍ (20 ደቂቃ)
(መ. በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማና በትራፊክ መብራት ላይ ቀለሞቹ ምን እንደሚወክሉ በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ ላይ እንዲጽፉ
ያድርጉ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን ያሟላሉ። መልስ፡- ቀይ በሰንደቅዓላማ ላይ “መስዋዕትነት መክፈልን” ሲያመለክት በትራፊክ መብራት
ደግሞ “ቁም” ማለትን ይወክላል።]

2.3.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (20 ደቂቃ)


(መ. ቅጥያዎችን በተስማሚ ቃላት ላይ እንዲጨምሩ ያድርጉ። ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. ቅጥያዎቹን በተስማሚ ቃላት ላይ ይቀጥላሉ። ምሳሌ፡- ድርቅ- ኦሽ = ድርቆሽ]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. አያያዥ ቃላቱን በመጠቀም ድርብ ዓረፍተነገሮች እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. አያያዥ ቃላትን በመጠቀም ድርብ ዓረፍተነገር ይጽፈሉ።]

22 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 የመንገድ ደህንነት !2


ምዕራፍ መረዳዳት
3

የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
ƒƒ የቀረበውን ምንባብ አዳምጠው ስሜታቸውን ያንፀባርቃሉ፤
ƒƒ ለክፍል ደረጃው በሚጠበቅ የፍጥነት መጠን ምንባቦችን ያነባሉ፤
ƒƒ ቅጥያዎችን የያዙ ቃላትን በመጠቀም አረፍተነገር ይመሠርታሉ፤
ƒƒ ድርብና ድብልቅ ዓረፍተነገሮችን ይፅፋሉ።

3.1.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) ድር ቢያብር

ድር ቢያብር

እኛ ኢትዮጵያዊያን ውብ ባህል አለን። ከውብ ባህላችን መገለጫዎች መካከል አንዱ መረዳዳት ነው። መረዳዳት በልዩልዩ መንገዶች
ይከናወናል። ይኸውም በገንዘብ፣ በጉልበት፣ በሐሳብ ወዘተ ሊሆን ይችላል።

ገንዘብ የሌላቸው ሰዎች በብዙ መልኩ ሊቸገሩ ይችላሉ። መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን ማሟላት ሊሳናቸው ይችላሉ። ስለሆነም የእለት
ጉርስ የዓመት ልብስ በመስጠት ልንረዳቸው ይገባል። አምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ ነው፤ ለአምሳ ሰው ግን ጌጡ ነውና ከተባበርን
ችግሩን እናቀልላቸዋለን። በመኖሪያ ቤት እጦት ወይም በእርጅና ምክንያት የሚቸገሩ በርካታ ወገኖች አሉንና ልንደርስላቸው ይገባል።

አቅመ ደካማ የሆኑ ሰዎችን በጉልበታችን የምናግዝባቸው ብዙ አማራጮች አሉን። አንደኛው አማራጭ የመኖሪያ ቤታቸውን
በመስራት ወይም በማደስ መርዳት ነው። ሰዎች አቅም በማጣት የደረሰ አዝመራቸውን በወቅቱ መሰብሰቡ ሊያቅታቸው ይችላል።
አዝመራቸው በወቅቱ ባለመሰብሰቡ የተነሳ ምርታቸው ሊቀንስባቸው ይችላል። ስለሆነም አዝመራቸውን በወቅቱ በማጨድ፣
በመሰብሰብና ምርቱን በማስገባት ማገዝ ኹለተኛው አማራጭ ሊሆን ይችላል።

ëëë እስካሁን ካዳመጣችሁት ታሪክ ምን ተማራችሁ? ëëë

በእድሜ አንጋፋ የሆኑ ሰዎች አቅም ሊያንሳቸው፤ አይናቸውንም ሊከልላቸው ይችላል። መንገድ ላይ ሲንቀሳቀሱ የሌሎችን ድጋፍ
ይፈልጉም ይሆናል። በዚህ ወቅት መንገድ በማሻገርና በማመላከት መርዳት ይጠበቅብናል።

ሰዎች አብዛኛውን ጊዜ ከሌሎች ምክር ይሻሉ። አንድን ጉዳይ ለምን፣ እንዴትና መቼ ማከናወን እንዳለባቸው ለመወሰን የሌሎችን
ሐሳብ ይፈልጋሉ። በዚህ ጊዜ ጠቃሚ ሐሳብ በመስጠት ልንረዳቸው ይገባናል። እንዲህ ሲሆን ነባሩን የመረዳዳት ባህል ማስቀጠል
እንችላለን።

23 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 3 መረዳዳት !3


ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. ከጓደኞቻቸውጋር በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ያደርጋሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ድር ቢያብር የሚለውን ታሪክ ረጋ ብለው ኹለት ጊዜ ያንብቡላቸው። ታሪኩን እየገመቱ እንዲያዳምጡ ያድርጉ። የማዳመጥ
ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ንባብዎን ለአፍታ ያህል ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ምላሻቸውን ካዳመጡ በኋላ
ንባብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ ተማሪዎች በጥንቃቄ ያዳምጣሉ፤ ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንደአስፈላጊነቱ የማስተካካያ ግብረመልስም ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ይሠራሉ። ለምሳሌ፡- 1. ሀ. [መ. መረዳዳት ነው።]
(መ. የለ ጥያቄ አመራማሪ ስለሆነ የሚያስቡትን እንዲናገሩ ያድርጉ።)
(መ. 2ኛውን ጥያቄ ከምንባቡ ውስጥ በማየት የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን እንዲሞሉ ያድርጉ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን ያሟላሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በሳጥኑ ውስጥ የቀረቡትን ቃላትና ሐረጋት ከሀ-ሠ ካሉት ቃላትጋር በማስማማት እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላትንና ሐረጋትን ያዛምዳሉ።] [ተ. በዕድሜ አንጋፋ]
[ተ. የቤት - እጦት] [ተ. ውብ- ባህል]
[ተ. የገንዘብ - ድጋፍ] [ተ. አዕምሮ- ማደስ]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. አሁን አቀላጥፈው የሚያነቡበት ሰዓት ነው። “አዝመራን በህብረት” የሚለውን ታሪክ ሞዴል ሆነው ካነበቡላቸው በኋላ
በጥንድ እየተቀባበሉ አቀላጥፈው እንዲያነቡ ያድርጉ። አቀላጥፈው የማያነቡ ተማሪዎችንም ያግዙ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ አቀላጥፈው ያነባሉ።]

3.1.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ) ህጻኑ ተስፋዬ

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. ታሪኩን ከማንበባቸው በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ይወያያሉ።]

24 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 3 መረዳዳት !4


የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)
(መ. “ህጻኑ ተስፋዬ” የሚለውን ታሪክ ለመገንዘብ በለሆሳስ እንዲያነቡ ያድርጉ። ማንበባቸውንም ይከታተሉ።)
[ተ. “ህጻኑ ተስፋዬ” የሚለውን ታሪክ ድምጻቸውን ሳያሰሙ ለመረዳት ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። መልሳቸውን ተራበተራ ለክፍሉ ያጋሩ። እንደአስፈላጊነቱ የማስተካከያ
ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]
ለምሳሌ፡- (ተ . በትምህርቱ ጎበዝና በስነምግባሩ ምስጉን ስለሆነ።)

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ቃላቱን ከተቃራኒያቸው ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ተቃራኒ ቃላትን ያዛምዳሉ። መልስ 2. መ 4. ሀ]

መጻፍ (10 ደቂቃ)


(መ. በትርፍ ጊዜያቸው ቤተሰቦቻቸውን እንዴት እንደሚያግዙ የሚገልጽ አጭር አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ቤተሰቦቻቸውን እንዴት እንደሚያግዙ አጭር አንቀጽ ይጽፋሉ።]

3.1.3 ማዳመጥ (20 ደቂቃ)


(መ. ለማስታወስ ይረዳቸው ዘንድ “ድር ቢያብር” የሚለውን ታሪክ ደግመው ያንቡላቸው፤
[ተ. ታሪኩ ተደግሞ ሲነበብላቸው በጥንቃቄ ያዳምጣሉ።]
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ለተሰመረባቸው ቃላት በፍቺ የሚስማማቸውን ቃል መርጠው እንዲመልሱ ያድርጉ)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላት ተመሳሳያቸውን በመምረጥ ያዛምዳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “አዝመራን በህብረት” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ አቀላጥፈው እንዲያነቡ ያለማምዷቸው። አርዓያ ሆነው ታሪኩን
በድጋሚ ያንብቡላቸው።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ ሆነው እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ማንበብን ይለማመዳሉ።]

25 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 3 መረዳዳት !5


3.1.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላት ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጉ።)
[ተ. በቃላቱ ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ፤ የሠሩትን ዓረፍተነገር ለመምህር ያሳያሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. የተጓደለውን አንቀጽ አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ የጻፉትን አንቀጽ ያንብቡ።) እንደሚከተለው ሊጽፉ ይችላሉ።)
[ተ. የተጓደለውን አንቀጽ አሟልተው ይጽፋሉ።] ለምሳሌ፤-
[ተ. የአጎቴ ቤት ስራ ዛሬ ነው። ብዙ ሰው ተሰብስቧል። ኹለት ሰዎች ከላይ ወጥተው ማገር ይመታሉ፤ ሌሎች ደግሞ ቆርቆሮና
ማገር ያቀብላሉ። መጋዝ የያዙት ሰዎች ደግሞ እንጨቱን እየለኩ ይቆርጣሉ። አብዛኛው ሰው ለግድግዳ የሚሆን ጠርብ
ከውጪ ወደቤት እየተሸከመ ያስገባል። ባራቱም ማዕዘን ሚስማር የሚመቱ ሰዎች ይታያሉ። ማንም ስራ አልፈታም። ልክ
ከቀኑ በዘጠኝ ሰዓት ቤቱ ቆርቆሮ ለብሶ አለቀ።]

3.1.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(1ኛ. መ. በቃላቱ ላይ አብዢ ምዕላዶችን ጨምረው እንዲጽፍ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. አብዢ ምዕላዶችን በቃላት ላይ ይጨምራሉ።]
(2ኛ መ. በታሪኩ መሠረት ለቃላቱ አውዳዊ ፍች እንዲሰጡ ያድርጉ)
[ተ. ለቃላት አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ። በረከት- ስጦታ፤ ምርቃት- መልካም ምኞት፤ አዋቂ- ትልቅ ሰው]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. ቤቱ የጠፋበት ህፃን መንገድ ላይ ቢያገኙ እንዴት ሊረዱት እንደሚችሉ የሚገልፅ አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ። ሐሳባቸውን
እንዴት ማደራጀት እንዳለባቸው ያብራሩላቸው።
[ተ. ቤቱ የጠፋበት ህፃን መንገድ ላይ ቢያገኙ እንዴት ሊረዱት እንደሚችሉ የሚገልፅ አንቀጽ ይፅፋሉ።]

3.2.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) አርሶአደሮቹ

አርሶአደሮቹ

የአገራችን አርሶአደሮች ብልሆች ናቸው። ሥራዎቻቸውን መቼና እንዴት ማከናወን እንዳለባቸው ያውቃሉ። የእርሻ መሬታቸውን
በወቅቱ ያርሳሉ፤ ያለሰልሳሉ። በየዓመቱ ለመሬቱ ተስማሚ የሆነ የእህል ዓይነት እያፈራረቁ ይዘራሉ። አረም እንዳይውጠው
ተከታትለው ያርማሉ። አዝመራው ሲደርስ ያጭዳሉ፤ ምርታቸውን ወደጎተራ ያስገባሉ።

26 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 3 መረዳዳት !6


ይህን ሁሉ ተግባር የሚያከናውኑት ርስበርስ በመረዳዳት ነው። ሥራን በህብረት የማከናወን ተግባር ደቦ ይባላል። ደቦ ሥራን በወቅቱ
ለማከናወን ያስችላል። በጋራ እየተረዳዱ የመስራት ባህልን ያሳድጋል። ፍቅርና መተሳሰብንም ይጨምራል።

ëëë ሌላስ በምን በምን ተግባር የሚረዳዱ ይመስላችኋል? ëëë

የአገራችን አርሶአደሮች ቤት ለመስራት ሲፈልጉም ርስበርስ ይረዳዳሉ። በተናጠል ለማከናወን የሚያስቸግራቸውን ወይም
የማይቻላቸውን ተግባር በቀላሉ ለመፈፀም መረዳዳት እንደሚያስፈልጋቸው ያውቃሉ። በሌላም በኩል የአንዱን ጉድለት ሌላኛው
እየሞላ መኖርንም ተለማምደውታል። ስለሆነም አንድ በሬ ብቻ ያለው ገበሬ የጎረቤቱን በሬ ወስዶ ሲያርስ ይውላል። በሌላ ቀን
ደግሞ የራሱን በሬ ለጎረቤቱ ይሰጠዋል፤ ጎረቤቱ ሲያርስ ይውላል። የዘር እህል ሲቸግራቸውም ርስበርስ ይረዳዳሉ። ያለው ለሌለው
ይሰጠዋል፤ ያበድረዋል። ተበዳሪውም ምርቱን ሲሰበስብ አመስግኖ ይመልሳል።

በአጠቃላይ ልባሞቹ ገበሬዎች በመረዳዳት እንጅ በተናጠል ኑሮን መግፋት እንደማይቻል ጠንቅቀው ያውቃሉ። ስለሆነም ርስበርስ
መረዳዳትን ባህል አድርገውታል።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ። ታሪኩን ማንበብ ከመጀመርዎ በፊት የሐሳብ
ማደራጃ ቢጋሩን በደብተራቸው ላይ አዘጋጅተው የታሪኩን ርዕስ ተመልክተው ማወቅ የሚፈልጓቸውን ጉዳዮች እንዲጽፉ
ያድርጉ። ከዚያም ታሪኩን ሲያነቡላቸው እያዳመጡ ይቆዩና ከታሪኩ የተማሩትን እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ርስበርሳቸው ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ረጋ ብለው በጥሩ አነባበብ ያንብቡላቸው። እንዳስፈላጊነቱ ይድገሙላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ
ንባብዎን ለአፍታ ቆም አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው፤ መልሳቸውን ተቀብለው ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. የማዳመጥ ታሪኩን በጥሞና ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ማወቅ የምፈልገው እና ከታሪኩ የተማርኩት በሚሉት ርዕሶች ሥር ካዳመጡት ታሪክ በመነሳት ነጥቦችን እንዲጽፉ መግለጫ
ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ይመልሳሉ።]
[ምሳሌ፡- ደቦ - ስራን በህብረት የማከናወን ተግባር ፣ የዘር እህል - ለዘር የሚሆን እህል]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ለቃላቱ ተመሳሳይና ተቃራኒ ፍቺ ያላቸውን ቃላት እንዲጽፉ ያደርጉ።)
[ተ. ለቃላት ተመሳሳይና ተቃራኒ ፍቺ ይጽፋሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች የመርፌን፣ የክርንና የልብስን ንግግሮች ተከፋፍለው በትወና መልክ ታሪኩን እየተቀባበሉ እንዲያነቡ ያግዟቸው።
በቅድሚያ ከአንድ ተማሪ ጋር በትወና መልክ በማንበብ ያሳዩኣቸው።)
[ተ. “መርፌና ክር “ የሚለውን ታሪክ በትወና መልክ ያነባሉ።]

27 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 3 መረዳዳት !7


3.2.2 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. ታሪኩን ከማንበባቸው በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ይወያዩ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (5 ደቂቃ)


(መ. “ርግቧና ጭልፊቷ” የሚለውን ታሪክ ለመገንዘብ በለሆሳስ ያስነብቡ፤ ሁሉም ተማሪዎች ስለማንበባቸው እርግጠኛ ይሁኑ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. የታሪኩን ዋና ሐሳብ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ ላይ በቅደምተከተል እንዲጽፉ ያድርጉ። የጻፉት ትክክል ስለመሆኑ ይከታተሉ፤
እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. የታሪኩን ፍሰት በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ ውስጥ ይጽፋሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. የቀረቡትን ቃላት በክቡ ውስጥ ርግብ፣ የጋራ እና ጭልፊት በሚሉት ሥር እንዲመድቡ ያድርጉ።)
[ተ. ርግብ- ዛፍ፣ ማዘን፤ ጭልፊት - ዋሻ፣ ማጽናናት፤ የጋር- መረዳዳት፣ መጎራበት]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. የአንድ ክፍል ተማሪዎች እንዴት ሊረዳዱ እንደሚችሉ የሚገልፅ አንድ አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. የአንድ ክፍል ተማሪዎች እንዴት ሊረዳዱ እንደሚችሉ የሚገልፅ አንድ አንቀጽ ይጽፋሉ።]

3.2.3 ማዳመጥ (20 ደቂቃ)


(መ. ምንባቡን በድጋሚ አዳምጠው ዓረፍተነገሮቹን አሟልተው ይጽፋሉ።)
[ተ. ዓረፍተነገሮቹን አሟልተው ይጽፋሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ዓረፍተነገር መሥርተው ለቃላቱ አውዳዊ ፍች እንዲሰጡ ያድርጉ። ምሳሌ ሠርተው ያሳዩ።)
[ተ. ለቃላቱ አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “መርፌና ክር” የሚለውን ታሪክ በትወና መልክ እየተቀባበሉ እንዲያነቡ ያድርጉ። በዚህ ክፍል ለተገቢ አገላለፅ ትኩረት
ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በትወና መልክ ያነባሉ።]

28 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 3 መረዳዳት !8


3.2.4 መጻፍ (20 ደቂቃ)

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ከሁለቱ ክቦች ውስጥ በፍቺ ተመሳሳይ ቃላትን እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. በፍቺ ተመሳሳይ ቃላትን መርጠው ያዛምዳሉ።]

መጻፍ (30 ደቂቃ)


(መ. ወንዝ የሞላበት ነጋዴና ዋናተኛው” በሚል ርዕስ ባለኹለት አንቀፅ ታሪክ ፈጥረው እንዲጽፉ ያድርጉ። በመጀመሪያ ስለዋናተኛና
ወንዝ ሞልቶበት ስለተቸገረ ነጋዴ እንዲያስቡ ያድርጉ፤ ከዚያም ከአዕምሯቸው ሐሳብ እያመነጩ የፈጠራ ድርሰት እንዲጽፉ
ያድርጉ። የጻፉትንም በክፍል ውስጥ እንዲያነቡ በማድረግ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ከአዕምሯቸው ሐሳብ እያመነጩ የፈጠራ ድርሰት ይጽፋሉ።]

3.2.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. በሳጥኑ ውስጥ ያሉትን ቅጥያዎች በተስማሚ ቃላት ላይ እንዲጨምሩ ያድርጉ።)

[ተ. መጥረግ - ኢያ = መጥረጊያ] [ተ. ቤት - ኣቸው = ቤታቸው]


[ተ. ሰርግ - ኧኛ = ሰርገኛ] [ተ ልብ - ኣም =ልባም]
[ተ. ሰላም -ኣዊ = ሰላማዊ]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. “ገጣሚና አዝማሪ” በሚል ርዕስ አንድ የተሟላ አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ። የጻፉትን አንቀጽ በክፍልውስጥ እንዲያቀርቡ
በማድረግ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ገጣሚና አዝማሪ በሚል ርዕስ አንድ የተሟላ አንቀጽ ይጽፋሉ።]

3.3.1 ማዳመጥ (20 ሰዓት) የእማማ ቤት

ወቅቱ ክረምት በመሆኑ ዝናብ ወደቤታቸው ይገባል። በላስቲክ ለመከለል ቢሞክሩም ነፋሱ እያነሳ ይወስድባቸዋል። የቤቱ ወለል
እንደውጩ ሁሉ ጭቃ ሆኗል። የቤቱ ቅዝቃዜ ከውጩ የተለየ አይደለም። እማማ በዚች ደሳሳ ቤት ውስጥ ብቻቸውን ለረጅም
ዓመታት ኖረውባታል። ሆኖም እንደአሁኑ የተሰቃዩበት ጊዜ አልነበረም። ቤቷ እንደእማማ ከዓመት ዓመት እያረጀት ሄዳለች። ከላይ
ዝናብ፣ ከጎን ወጨፎ፣ ከመሬት ጎርፍ ይገባል። እማማ ጉልበትም ሆነ ገንዘብ ስለሌላቸው ቤታቸው ሲፈርስ ከማየት ውጪ ምንም
አማራጭ አልነበራቸውም።
ëëë
የእማማ ዕጣ ፈንታ ምን የሚሆን ይመስላችኋል?ëëë

29 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 3 መረዳዳት !9


እኔና ጓደኞቼ የእማማን ቤት ዝም ብለን ለማየት ህሊናችን አልፈቀደም። ትናንት ረፋድ ላይ በሰፈር ተሰብስበን መወያየት ጀመርን።
የእማማን ቤት ለማደስ ወሰንን። በእኛ አቅም ብቻ የሚታደስ አይደለም። እንጨት፣ ቆርቆሮና ሚስማር እንዲረዳን የአካባቢውን
ነዋሪ ጠየቅን። በቂ እንጨትና ቆርቆሮ አገኘን። ከዚያም ከጓደኞቼ ጋር እየተረዳዳን የእማማን ቤት ዛሬ አደስንላቸው። በተጨማሪም
በዝናብ የተበላሹባቸውን አንዳንድ የቤት እቃዎች ገዝተን ተካንላቸው።

እማማ እንደዛሬ ሲደሰቱ አይቻቸው አላውቅም። በጤና፣ በፍቅርና በሰላም እንድንኖር መረቁን። እኛም በእማማ ደስታ እርካታ
ተሰማን። ርስበርስ ስንረዳዳ ብዙ መስራት እንደምንችልም ተገነዘብን።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. ታሪኩን ከማዳመጣቸው በፊት በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. የሚከተለውን ታሪክ ረጋ ብለው ኹለት ጊዜ ያንብቡላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ንባብዎን ገታ አድርገው
ጥያቄውን ይጠይቋቸው፤ መልሳቸውን ተቀብለው ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ በጥሞና ያዳምጣሉ፤ ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ካዳመጡት ታሪክ ተነስተው የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ የማስተካከያ ግብረመልስ
ይስጧቸው።)
[ተ. ታሪኩን አዳምጠው ሲጨርሱ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው ይጽፋሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. የቃላቱን አውዳዊ ፍቺ ዓረፍተነገር መሥርተው እንዲያሳዩ ያድርጉ።)
[ተ. የቤቱን ግድግዳ ወጨፎ ስለመታው ጭቃው ረግፏል።]
[ተ. ከሰው ሀገር ህንጻ የራስ ሀገር ደሳሳ ጎጆ ትበልጣለች።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “አርኣያነት” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ፤ አነባበባቸውን
እየተከተሉ ማስተካከለያ ይስጧቸው።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

30 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 3 መረዳዳት V


3.3.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ። ተማሪዎች የአንብቦ መረዳት ጥያቄውን በአግባቡ
መመለስ እንዲችሉ በቅድሚያ ሠንጠረዡን በደብተራቸው እንዲያዘጋጁና ከርዕሱ በመነሳት የሚያውቁትንና ማወቅ
የሚፈልጉትን ጉዳይ በሰንጠረዡ ውስጥ እንዲፅፉ ያድርጉ። በማስከተልም የተማርኩት የሚለውን አምድ ታሪኩን ካነበቡ
በኋላ እንዲሞሉ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ይወያያሉ። ሠንጠረዡን በደብተራቸው በማዘጋጀት የሚያውቁትንና ማወቅ
የሚፈልጉትን ጉዳይ ይመዘግባሉ።]

ማንበብ (7 ደቂቃ)
(መ. “ያገርልጅ የማርእጅ” የሚለውን ታሪክ ለመረዳት ድምጽ ሳያሰሙ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. ባነበቡት ታሪክ መሠረት የቢጋር ሠንጠረዡን አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።
ለምሳሌ የሚከተለውን መጠቀም ይችላሉ።)
[ተ. ባነበቡት ታሪክ መሠረት “የተማርኩት” የሚለውን የቢጋር ሠንጠረዡን ክፍል አሟልተው ይጽፋሉ።]

የማውቀው ለማወቅ የምፈልገው የተማርኩት


ƒƒ ሴቶች ወደዐረብ ሀገር እንደሚሄዱ ƒƒ ወደዐረብ ሀገር ሄደው ምን እንደሚሰሩ ƒƒ ረፍት የለሽ ስራ ይሠራሉ
ƒƒ ችግር ይደርስባቸዋል

ቃላት (8 ደቂቃ)
(መ. ለተሰመረባቸው ቃላትና ሐረጋት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ፤ እንደአስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. ለቃላቱና ለሐረጋቱ አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ።]

መጻፍ (12 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን ነጥቦች መሠረት በማድረግ ሐሳቡን አስፋፍተው ታሪክ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. የተሰጡትን ሐሳቦች መነሻ በማድረግ ሐሳቡን አስፋፍተው ታሪክ ይጽፋሉ።]

3.3.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)


(መ. “የእማማ ቤት” የሚለውን ታሪክ እንዲያስታውሱ ደግመው ያንብቡላቸው፤ በመቀጠልም የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን
ይጠይቋቸው።)
[ተ. ታሪኩን ደግመው በማዳመጥ የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በቃላቸው ይመልሳሉ።]

31 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 3 መረዳዳት V1


ቃላት (10 ደቂቃ)
(መ. በተሰጡት ቃላትና ሐረጋት ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጉ።)
[ተ. በቃላቱና በሐረጋቱ ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (15 ደቂቃ)


መ. (“አርአያነት” የሚለውን ታሪክ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ከርስዎ ጋር እየተቀባበሉ እንዲያነቡ ያድርጉ። በዚህ
ክፍል ታሪኩን ያለስህተት ማንበባቸውን ትኩረት ሰጥተው ይከታተሉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ታሪኩን በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እየተቀባበሉ ያነባሉ። ]

3.3.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. ቃላቱንና ሐረጋቱን ከተመሳሳያቸው ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. “ያገርልጅ የማር እጅ” የሚለውን ታሪክ በአንድ አንቀጽ አሳጥረው እንዲጽፉ ያድርጉ። በቀረበው ማስታወሻ ላይ ማብራሪያ
ይስጡ።)
[ተ. ያገር ልጅ የማር እጅ የሚለውን ታሪክ በአንድ አንቀጽ አሳጥረው ይጽፋሉ።]

3.3.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ቅጥያዎቹን በተስማሚ ቃላት ላይ እንዲቀጥሉ ያድርጉ።)

[ተ. ሀብታ - ኣም = ሀብታም] [ተ. ድርቆ -ኧት = ድርቀት]


[ተ. ጤና -ኣማ = ጤናማ] [ተ. መጥረብ -ኢያ = መጥረቢያ]

መጻፍ (30 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች ሐሳባቸውን እየተጋሩ ጅምሩን አንቀጽ አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ ሲጨርሱ ማስተካከያ ይስጧቸው። በሐሳብ
ፍሰቱ ላይ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ጅምር አንቀጹን አሟልተው ይጽፋሉ።]

32 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 3 መረዳዳት V2


ምዕራፍ ሥርዓተፆታ
4

የምዕራፉ ዓላማዎች

ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-


ƒƒ በምንባቡ የቀረበውን ርዕሰ ጉዳይ አዳምጠው ስሜታቸውን ያንፀባርቃሉ፤
ƒƒ የምንባቡን ዝርዝር መረጃዎች አንብበው መልሰው ይፅፋሉ፤
ƒƒ ግሶችን ተጠቅመው አረፍተነገር ይመሠርታሉ፤
ƒƒ የአንቀፅን ፅንሰሐሳብ ያብራራሉ።

4.1.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) እኩል ተሳትፎ እኩል ድርሻ

እኩል ተሳትፎ እኩል ድርሻ

አንዳንድ ሰዎች የሴትና የወንድ ስራ የተለያየ መስሎ ይታያቸዋል። በዚህም ሴትን ደካማ ወንድን ጠንካራ አድርገው ያስባሉ።
ከጥንት ጀምሮ ወንድ በአደን፣ ሴት በምግብ ማብሰል ሲሳተፉ ነበር። ወንዶች በእርሻና በንግድ ሲሰማሩ ሴቶች በጉልጓሎና
በአረም በወፍጮና በፈትል እንደሚሰማሩ ይታወቃል። ይህ የሆነው ከልማድና ከባህል የተነሳ እንጂ በተፈጥሮ የስራ ክፍፍል ስላለ
አይደለም። በእርግጥ ተፈጥሯዊ በሆነ መልኩ ሴት አርግዛ፣ አምጣና ወልዳ እንዲሁም አጥብታ ልጅ ታሳድጋለች። በዚህ የተነሳ
ጉልበቷ ሊቀንስ ስለሚችል ከባድ ስራ ለመስራት ትቸገር ይሆናል።

ëëë እስካሁን ካዳመጣችሁት ምን ተረዳችሁ? ëëë

ጊዜው እየዘመነ ስልጣኔ እየተስፋፋ በመጣ ቁጥር ግን የሴቶች እኩልነት ህግና ደንብ ወጥቶለት ተግባራዊ ሊደረግ ይችላል።

ባህሉ ካልተጫናቸው በስተቀር ሴቶች በሬ ጠምደው ያርሳሉ፤ ሸማ ይሠራሉ፤ አናጺና ግንበኛ በመሆን ቤታቸውን ይሠራሉ።
ለዚህም በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን በፎገራ ወረዳ የሚገኘውን የአውራአምባ ማኅበረሰብ ለአብነት መጥቀስ ይቻላል። በዚህ
ማኅበረሰብ ወንዶች ልጅ ያዝላሉ፤ እህል ይፈጫሉ፤ እንጀራ ይጋግራሉ፤ ጥጥ ይፈትላሉ፤ ውኃ ይቀዳሉ። ይህ ያንች ስራ ነው፤
ይህ ደግም ያንተ ስራ ነው በማለት አይገፋፉም። ማንኛውንም ስራ በእኩል ተሳትፎ ያከናውናሉ፤ ከሚገኘው ውጤትም በእኩል
ድርሻ ተጠቃሚ ይሆናሉ።

33 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ V3


ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. ተማሪዎች ታሪኩን ከማዳመጣቸው በፊት በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከጓኞቻቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ረጋ ብለው በጥሩ አነባበብ ያንብቡላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ንባብዎን ገታ አድርገው ጥያቄውን
ይጠይቋቸው፤ መልሳቸውን ተቀብለው ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. ታሪኩ ሲነበብ በጥሞና ያዳምጣሉ፤ ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ፤ መልሳቸውን ለመምህር ያሳያሉ።]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. በሳጥን ውስጥ ያሉትን ቃላት የሴት ተግባራት፣ የወንድ ተግባራት ወይም የጋራ ብለው እንዲመድቡ ያድርጉ። በምድቦቹ ላይ
እንዲወያዩ ያድርጉ)
[ተ. በሳጥን ውስጥ ያሉትን ቃላት የሴት ተግባራት፣ የወንድ ተግባራት ወይም የጋራ ብለው ይመድባሉ፤ በምድቦቹ ላይ ርስበርስ
ይወያያሉ።]
(ማስታወሻ፡- የወንድ ብቻ የሚባል ተግባር የለም። የሴት ተግባራት ተፈጥሯዊ የሆኑት ማርገዝና ማጥባት ብቻ ናቸው።
ሌሎቹ ተግባራት የጋራ በሚለው ሥር ይሰፍራሉ።)
አቀላጥፎ ማንበብ (13 ደቂቃ)
(መ. “ክብር ለእናቶቻችን” የሚለውን ታሪክ በትወና መልክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ አቀላጥፈው
እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በትወና መልክ ጥንድ ሆነው እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

4.1.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ከማንበባቸው በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “ሴቶች ባደባባይ” የሚለውን ታሪክ ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው እንዲያነቡ መመሪያ ይስጡ። ሁሉም ተማሪዎች ታሪኩን
ስለማንበባቸው ክትትል ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ። ዋና ሐሳቡን እየተረዱ ያነባሉ።]

34 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ V4


ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ፤እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. የተሰመረባቸውን ቃላት በሳጥኑ ውስጥ ባሉ ቃላት በመተካት ዓረፍተነገሮቹን እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. የተሰመረባቸውን ቃላት በተመሳሳይ ቃላት ተክተው ይጽፋሉ።]

መጻፍ (13 ደቂቃ)


(መ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን መሠረት በማድረግ በገጠር ስለሚኖሩ እናቶች አጭር ታሪክ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን መሠረት በማድረግ በገጠር ስለሚኖሩ እናቶች አጭር ታሪክ ይጽፋሉ።)

4.1.3 ማዳመጥ (20 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. “እኩል ተሳትፎ እኩል ድርሻ” የሚለውን ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው።)
[ተ. ምንባቡ ሲነበብ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ዓረፍተነገሮቹን “እውነት “ ወይም “ሀሰት” ብለው በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። ለመልሳቸው ምክንያት እንዲሰጡ
ይጠይቁ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን እውነት ወይም ሀሰት በማለት በጽሑፍ ይመልሳሉ፤ በምክንያት ያብራራሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ አድርገው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ መመረያ ይስጡ።)
[ተ. በቃላቱ አውዳዊ ፍቺ ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ክብር ለእናቶቻችን” የሚለውን ታሪክ በትወና መልክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በጥሩ አገላለጽ እንዲያነቡ
ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ከአንድ ተማሪ ጋር አቀላጥፈው በማንበብ አርዓያ ሆነው ያሳዩ።)
[ተ. ታሪኩን በትወና መልክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

35 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ V5


4.1.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲያሳዩ አድርገው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ይዘዟቸው።)
[ተ. በቃላቱ አውዳዊ ፍቺ ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. “ሴቶችን ማስተማር ማህበረሰቡን ማስተማር ነው” በሚለው ሐሳብ የተሟላ አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ። በመጀመሪያ ረቂቅ
እንዲያዘጋጁ ያግዟቸው፤ በመቀጠልም አስተካክለው እንዲጽፉ ያድርጉ። )
[ተ. በተሰጠው መንደርደሪያ ዓረፍተነገር የተሟላ አንቀጽ ይጽፋሉ።]

4.1.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. ቅጥያዎችን ከቃላቱ በማውጣት ለያይተው እንዲጽፉ ያድርጉ። ምሳሌ ሠርተው ያሳዩኣቸው።)
[ተ. በዋናው ቃል ላይ የተቀጠሉትን ቅጥያዎች ለይተው ይጽፋሉ። ቅጥያዎቹን ለያይተው ይጽፋሉ።
ምሳሌ ጥንት-ኣዊ፣ ባህል -ኣችን]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች በየግላቸው ጅምር አንቀጹን ተገቢ ሐሳቦችን በማካተት አጠናቅቀው እንዲጽፉ ያድርጉ። ግብረመልስም
ይስጧቸው።)
[ተ. ጅምር አንቀጹን አሟልተው ይጽፋሉ።]

4.2.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) እኩልነት

እኩልነት

ብዙዎቻችን የሴቶችን አቅም ዝቅ አድርጎ የሚያይ የተዛባ አመለካከት ይዘን ቆይተናል። ከፍያለ ችሎታ የሚጠይቁ ወይም የተሻለ
ገቢ የሚያስገኙ ስራዎችን የወንድ ስራ አድርጎ መቁጠር የተለመደ ነበር። በትምህርት ዓለም እንደሳይንስና ሒሳብ የመሳሰሉትን
ትምህርቶች ለሴቶች ከባድ ለወንዶች ግን ቀላል አድርገው የሚያስቡም አንዳንድ ግለሰቦች ነበሩ። ነገር ግን ሴቶችም በሳይንስና
በሂሳብ ከወንዶች እኩል አቅም እንዳላቸው ጥናቶች ያሳያሉ። በተጨማሪም ዶክተር ሲባል ከወንድ ጾታ ጋር ነርስ ሲባል ደግሞ ከሴት
ጾታ ጋር እናዛምድ ነበር። አርሶአደርን ስናስብም ወንድ እንጂ ሴት በአዕምሯችን አትመጣም።

ëëë ሴቶች ከወንዶች እኩል የተሰማሩባቸውን የሥራ መስኮች ጥቀሱ ëëë

36 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ V6


ሴቶች ከወንዶች እንደማያንሱ የሚያሳዩ በርካታ ማስረጃዎች አሉ። ወደሆስፒታሎች ስንሄድ አያሌ ቁጥር ያላቸው ሴት ዶክተሮችን
ማግኘት እንችላለን። በዩኒቨርሲቲዎችም ብዙ ሴት ፕሮፌሰሮችን እንቆጥራለን። በአጠቃላይ ሴቶች ላይ ያለንን የተሳሳተ አመለካከት
ማስተካከል ይገባናል። ይህ ካልሆነ በሴቶች ተሳትፎ ሊገኝ የሚችለውን ከፍተኛ አስተዋጾ እናጣለን። በአንድ እጅ ማጨብጨብ
እንደማይቻል ሁሉ ያለሴቶች ተሳትፎ ስኬታማ መሆን አይቻልም። በወንዶች ተሳትፎ ብቻ ያደገ ሀገርም ሆነ ማኅበረሰብ አይገኝም።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. ታሪኩን ከማዳመጣቸው በፊት በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ውይይት ያደርጋሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ረጋ ብለው በጥሩ አነባበብ ያንብቡላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ንባብዎን ገታ አድርገው ጥያቄውን
ይጠይቋቸው፤ መልሳቸውን ተቀብለው ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. ታሪኩን መምህር ሲያነቡ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ፤ ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎች በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልሱ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ ውስጥ ያሉትን ቃላትና ሐረጋት ለሴቶች እኩልነት ምሳሌ የሚሆኑትንና ምሳሌ የማይሆኑትን ለይተው
እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ምሳሌ የሚሆኑ -ስኬታማነት ፣ ድንቅ ውጤት ፣ ጉልህ፣ ተሳትፎ]
[ተ. ምሳሌ የማይሆኑ- ወደማጀት፣ በወንድ ያልቅ]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “እኔና ልጆቼ” የሚለውን ታሪክ በቡድን ሆነው በትወና መልክ እየተቀባበሉ በትክክልና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ)
[ተ. “እኔና ልጆቼ” የሚለውን ታሪክ በቡድን ሆነው በትወና መልክ እየተቀባበሉ በትክክልና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

4.2.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ከማንበባችን በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ይወያያሉ።]

37 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ V7


የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)
(መ. “እማዬና አባዬ” የሚለውን ታሪክ ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው እንዲያነቡ ያድርጉ፤ ሁሉም ተማሪዎች ታሪኩን እያነበቡ
ስለመሆናቸው ይከታተሉ።)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው በለሆሳስ ያነባሉ።]

ድህረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎቹ ታሪኩን መሠረት አድርገው የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው ይጽፋሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. በተሰመረባቸው ቃላት ከታሪኩ ውጭ ባላቸው ፍቺ ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ መመሪያ ይስጡ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ
ይስጡ።)
[ተ. ላሚቱ ተጠምዳ ስለዋለች በጣም ደክሟታል።]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን ነጥቦች በማስፋፋት ኹለት አንቀጽ ጽፈው እንዲያቀርቡ ያድርጉ።)
[ተ. የቀረቡትን ነጥቦች በማስፋፋት ኹለት አንቀጽ ይጽፋሉ።]

4.2.3 ማዳመጥ (20 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. “እኩልነት” የሚለውን ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው።)
[ተ. ታሪኩ ሲነበብ በጥሞና ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ(10 ደቂቃ)
(መ. በታሪኩ መሠረት የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን “እውነት” ወይም “ሀሰት” ብለው እንዲመልሱ ያድርጉ፤ ለመልሳቸው ምክንያት
እንዲሰጡ ይጠይቋቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን እውነት ወይም ሀሰት በማለት ይመልሳሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. በ “ሀ” ክፍል ካሉት ቃላት ጋር አብረው የሚሄዱ ቃላትን ከ “ለ” ክፍል በመምረጥ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን ከተስማሚ ፍቻቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

38 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ V8


አቀላጥፎ ማንበብ (15 ደቂቃ)
(መ. “እኔና ልጆቼ” የሚለውን ታሪክ ትወናዊ በሆነ መልኩ እየተቀባበሉ በትክክልና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ። በቅድሚያ
ርስዎ ከጥሩ አንባቢ ተማሪዎች ጋር አርዓያ ሆነው ያንብቡላቸው።)
[ተ. ታሪኩን ትወናዊ በሆነ መልኩ እየተቀባበሉ በትክክልና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

4.2.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. የተሰመረባቸውን ቃላት ከታሪኩ ውስጥ ተመሳሳያቸውን በመፈለግ እንዲተኩ ያድርጉ።)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላት ከታሪኩ ውስጥ ተመሳሳያቸውን በመፈለግ ይተካሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. ጅምር አንቀጹን መነሻ አድርገው የተሟላ አንቀጽ እንዲጽፉ መመሪያ ይስጡ። የጻፉትን አንቀጽ በክፍል ውስጥ እንዲያነቡ
በማድረግ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የሚከተለውን ሊጽፉ ይችላሉ።]

ችግሩን ቀመስነው
ተ. የእናቴን የስራ ጫና አባታችንም ሆነ እኛ ተረድተነው አናውቅም። ለአፍታ እንኳ ሳታርፍ ጀምበሯ ትጠልቃለች። እንጨት ራሷ
ፈልጣ እንጀራ ትጋግራለች። ብዙ ሸክም አዝላ ወደገበያ ሄዳ ትመጣለች። ዛሬ ድንገት አመማትና ሆስፒተታል ሄደች። ዶክተሩ
ከሥራ ብዛት የተነሳ የልብ ድካም ህመም ስላመማት ለሳምንት ያህል ተኝታ እንድትታከም አዘዙ። እኛም እያዘንን ወደቤታችን
ሄድን። ቤቱ በጣም ቀዝቅዞ አገኘነው። ከሰል ማን ያያይዝ!፤ ምግብ ማን ይስራ! በጣም ራበን። መተያየት ብቻ ሆነ። ህጻኑ ልጅ
ማልቀስ ጀመረ። እናታችን የተሸከመችው ከባድ ኃላፊነት አሁን ገባን። ስራ ብናግዛት ኖሮ እንደማትታመም ተረዳን። ከዚህ
በኋላ ግን የየድርሻችንን መስራት እንዳለብን ተገንዝበናል።]

4.2.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ዋናውን ቃልና ቅጥያዎቹን በማገናኘት አንድ ቃል አድርገው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ እርስዎ በቅድሚያ አንድ ምሳሌ ሠርተው
ያሳዩአቸው።) መልስ

[ተ. ሀ. [መ. ሰማሁ -ኣቸው = ሰማኋቸው]


ለ. [መ. አራት -ኧኛ = አራተኛ]
ሐ. [መ. አየሁ -ኣት = አየኋት]
መ. [መ. ባለቤት -ኤ = ባለቤቴ]
ሠ. [መ. ማንበብ -ኢያ = ማንበቢያ]

39 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ V9


መጻፍ (30 ደቂቃ)
(መ. ግሶችን ተጠቅመው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ። ተማሪዎች በጣም አጫጭር
ዓረፍተነገሮችን ብቻ እንዳይጽፉ ቢያንስ ዐምስት ቃላት ያሉት እንዲሆን ያሳስቧቸው።)
[ተ. ግሶችን ተጠቅመው ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]
(መ. ስለግሶች 3ኛ ክፍል የተማሩትን እንዲያስታውሱ ሊያደርጉ ይችላሉ። ግሶች በዓረፍተነገር መጨረሻ እንደሚመጡ ሊገልጹላቸው
ይችላሉ። የቀረበውን ማስታወሻ በተመለከተ ያብራሩላቸው። በዚህ ተግባር የቀረቡት ግሶች ድርጊትን የሚገልጹ የድርጊት
ግሶች መሆናቸውን ልብ ይበሉ።)
(መ. “የገጠር እናቶች ድካም” በሚል ርዕስ እናቶች ከቀን እስከማታ የሚያከናውኗቸውን ተግባራት በመጥቀስ ኹለት አንቀጽ
እንዲጽፉ ያድርጉ። በቅድሚያ የእናቶችን የስራ ድርሻ በመዘርዘር ቢጋር እንዲያዘጋጁ ቀጥለው ረቂቅ እንዲጽፉ በመጨረሻም
የተስተካከሉ አንቀጾች እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[እናቶች ከቀን እስከማታ በርካታ ተግባራትን ሲያከናወኑ ይውላሉ። ከቤተሰቡ ቀድመው በጧት ይነሳሉ። ለቤተሰቡ አባላት
የሚበቃ ምግብ መጥነው ያዘጋጁሉ። ቤተሰቡ ቁርስ በልቶ ከተሰማራ በኋላ ወደቤት ማዘጋጀት ይሄዳሉ። ቀጥለው እንጨት
ይለቅማሉ። ውኃም ይቀዳሉ፤ ቀትር ላይ ምሳ አዘጋጅተውና ቡና አፍልተው ቤተሰባቸውን ይቀበላሉ፤ወይም ወደማሳ ምግብና
ውኃ ያደርሳሉ፡ ወዘተ…] ብለው ሲጽፉ ይችላሉ።
[ተ. በተሰጣቸው ርእስ ኹለት አንቀጽ ይጽፋሉ።]

4.3.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) ሴቶች በገጠርና በከተማ

በሴቶችና በወንዶች መካከል ያለውን ማህበራዊ ልዩነት ለማስቀረት ብዙ ጥረት ተደርጓል። ህግ እየተደነገገ፣ ደንብና መመሪያ
እየወጣ በሴቶች ላይ የሚደርሰው የስራ ጫና መቀነስ እንዳለበት በይፋ ታውጇል። የተገኘው ተግባራዊ ለውጥ ግን አጥጋቢ
አይደለም። በተለይ የገጠሩ አካባቢ ከከተማው ጋር ሲነጻጸር ልዩነቱ ሰፊ ነው።

እስካሁን ድረስ በገጠር በሚኖሩ እናቶቻችን ላይ ያለው የስራ ጫና የከፋ ነው። ሴቶች በረሃ ወርደው እንጨት ይለቅማሉ።
ሁሉንም ባያካትትም በእጃቸው ይፈጫሉ። የቀንድ ከብት በረት፣ የጋማ እንስሳት ጋጥ ፣ የፍየልና የበግ ጉረኖ ያጸዳሉ። ሌሊቱን
በቂ እንቅልፍ ሳያገኙ ለቀጣዩ ቀን የሚሆን ምግብ ሲያዘጋጁ ያድራሉ። በጧት ሁሉንም እንደየባህሪው ቤት ባፈራው እህልውኃ
አስተናግደው ይሸኛሉ። በቤት ውስጥ ከሚሰሩት ስራ በተጨማሪ በውጪ ከአባወራው ጋር እኩል ሲደክሙ ውለው የሚመለሱት
በምሽት ነው። በተለይ ዘር በሚዘራበት፣ አዝመራ በሚታረምበትና በሚሰበሰብበት ወቅት ያለባቸውን የሥራ መደራረብ በቃላት
መግለጽ ያስቸግራል። በገጠር ሴት ልጆችን ወደትምህርት ቤት የመላክ ባህል ቢሻሻልም ከከተማው ጋር ሲታይ ገና ብዙ ይቀረዋል።
ያለዕድሜና ያለአቻ ጋብቻም እስካሁን አልተገታም።

ëëë የከተማ ሴቶች እነዚህ የስራ ጫናዎች ያሉባቸው ይመስላችኋል? ëëë

ወደከተማ ሴቶች ህይወት ስንመለስ በግብርናው ዘርፍ ከሚኖሩ የስራ ጫናዎች ነጻ ናቸው። ስልጣኔ በመምጣቱ የምግብ ማብሰል
ተግባራት በኤሌክትሪክ ኃይል ስለሚከናወን ድካማቸውን ቀንሶላቸዋል። ወንድ ሴት ሳይሉ ሁሉንም ልጆቻቸውን እኩል
ያስተምራሉ። ሴቶች በአለባበስና በንጽህና ከወንዶች አይተናነሱም። ህጻናትንና ጠቅላላ ቤተሰቡን የመንከባከብ ሁኔታም እኩል
ነው ለማለት ባያስደፍርም ወንዶችም እየተጋሩት ነው።

40 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ #


ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. ታሪኩን ከማዳመጣቸው በፊት በቅድመማዳመጥ ጥያቄው ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄው ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ረጋ ብለው በጥሩ አነባበብ ያንብቡላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ንባብዎን ገታ አድርገው ጥያቄውን
ይጠይቋቸው፤ ከመለሱ በኋላ ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. ታሪኩ ሲነበብ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ያዳመጡትን ታሪክ መሠረት አድርገው የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በማወዳደርና በማነጻጸር እንዲያሟሉ ያድርጉ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው ይጽፋሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ተመሳሳይ ፍቺ ያላቸውን ቃላት እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳይ ፍቻቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ሴቶችና ጎጂ ልማዶች” የሚለውን ታሪክ በትወና መልክ እየተቀባበሉ አቀላጥፈው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. የእናትንና የልጅን ንግግር በማስመሰል ታሪኩን አቀላጥፈው ያነባሉ።]

4.3.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. “የከተማችን ከንቲባ” የሚለውን ታሪክ ከማንበባቸው በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ
ያድርጉ።
[ተ. ታሪኩን ከማንበባቸው በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “የከተማችን ከንቲባ” የሚለውን ታሪክ በየግላቸው በለሆሳስ እንዲያነቡ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

41 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ #1


ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)
(መ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን ከታሪኩ ውስጥ ተገቢ ሐሳቦችን በማውጣት እንዲያሟሉ ያድርጉ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው ይጽፋሉ።]

ቃላት (8 ደቂቃ)
(መ. በዓረፍተነገሮቹ ለተሰመረባቸው ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ።)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላት አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ]

መጻፍ (12 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን ሐሳቦች መነሻ በማድረግ ስለመምህር አፀደ የተሟላ አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ። ሐሳቦቹን እንዴት ማስፋፋት
እንደሚቻል አንዱን ሐሳብ አስፋፍተው ያሳዩኣቸው።
[ተ. መነሻ ሐሳቦቹን መሠረት አድርገው የተሟላ አንቀጽ ይጽፋሉ።]

4.3.3 ማዳመጥ (10 ደቂቃ)

ድኅረማዳመጥ
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎች ባዳመጡት ታሪክ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

መናገር (10 ደቂቃ)


(መ. በዚህ ደረጃ ትኩረት የሚሰጠው የተማሪዎች የመናገር ክሂል ነው። ስለሆነም “የከተማ ሴቶች ምንም አይነት የስራ ጫና
የለባቸውም” በሚለው ርዕስ ላይ እንዲከራከሩ ያድርጉ።)
[ተ. የተሰጠውን መከራከሪያ ሐሳብ መነሻ በማድረግ ክርክር ያደርጋሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላትና ሐረጋት አውዳዊ ፍች ዓረፍተነገር እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. በተሰጣቸው ቃላትና ሐረጋት አረፍተነገር ይሠራሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ሴቶችና ጎጂ ልማዶች” የሚለውን ታሪክ በትወና መልክ እየተቀባበሉ አቀላጥፈው እንዲያነቡ ያድርጉ። ርስዎ ከአንድ ተማሪጋር
በማንበብ አርአያ ይሁኗቸው።)
[ተ. የእናትንና የልጅን ንግግር በማስመሰል ታሪኩን አቀላጥፈው ያነባሉ።]

42 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ #2


4.3.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በ “ሀ” ክፍል የቀረቡትን ቃላትና ሐረጋት በ “ለ” ክፍል ካሉት ተመሳሳያቸው ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

መጻፍ (30 ደቂቃ)


መ. (“የከተማችን ከንቲባ” የሚለውን ታሪክ ጭብጥ በሦስት ዓረፍተነገሮች አሳጥረው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን አሳጥረው በሦስት ዓረፍተነገሮች ይጽፋሉ።]
መ. (ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሴቶች ላይ ይደርሱ የነበሩ ጭቆናዎች እየቀነሱ መጥተዋል በሚል መንደርደሪያ አረፍተነገር አንድ
የተሟላ አንቀጽ ያጽፏቸው።)
[ተ. ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሴቶች ላይ ይደርሱ የነበሩ ጭቆናዎች እየቀነሱ መጥተዋል በሚል መንደርደሪያ አረፍተነገር አንድ የተሟላ
አንቀጽ ያጽፋሉ።]

4.3.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. በግሶቹ ላይ ቅጥያዎችን በመጨመር እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. በግሶቹ ላይ ቅጥያዎችን በመጨመር ይጽፋሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. ጅምር አንቀጹን አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ የጻፉትን ሊያነቡ ይችላሉ)
[ተ. ሴቶች በወንዶች የሚደርስባቸው ጭቆና በደል የቀነሰ ሊመስለን ይችላል። ነገር ግን አሁንም የግፍ ቀንበር ተሸክመው የሚኖሩ
ሴቶች ብዙ ናቸው። በሴቶች ላይ የሚደርሱ በደሎች አይነታቸው ብዙ ነው። ለአብነት ያህል የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል።
ዛሬም ድረስ በወንዶች እየተደበደቡ አካላቸው ላይ ጉዳት የሚደርባቸው ሴቶች ብዙ ናቸው። ያለፍላጎታቸው በኃይል
ተጠልፈው ወይም በቤተሰብ አስገዳጅነት ከማይፈልጉት ሰው ጋር መራራ ኑሮ የተጋፈጡም ሞልተዋል። ጉልበታቸውን
የጨረሱበትንና እድሜ ልካቸውን የለፉበትን ሀብትና ንብረት በአግባቡ ሳይካፈሉ ከሞቀ ቤታቸው የሚሰናበቱትን ቤት
ይቁጠራቸው። በአጠቃላይ ስለሴቶች መብት መከበር የተጻፈውንና በየመድረኩ የሚወራውን ያህል የመጣው ለውጥ እዚህ
ግባ የሚባል አይደለም።]

43 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 ሥርዓተፆታ #3


ምዕራፍ ጉብኝት
5

የምዕራፉ ዓላማዎች

ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-


ƒƒ ስለቱሪዝም መስህብ ቦታዎች የሰሙትን በቃል ዘገባ መልክ ያቀርባሉ፤
ƒƒ ምንባቡን አንብበው ሐሳቡን ያብራራሉ፤
ƒƒ አዳዲስ ቃላትን (ተዘውታሪ ቃላትን) በመጠቀም አረፍተነገር ይመሠርታሉ፤
ƒƒ በሚመሰርቷቸው ዓረፍተነገሮች ውስጥ ቅጽሎችን ይጠቀማሉ።

5.1.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) የአቡነ አሮን ገዳም

የአቡነ አሮን ገዳም

የአቡነ አሮን ገዳም በመቄት ወረዳ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ከወልድያ ወደጎንደር አቅጣጫ 150 ኪሎሜትር ርቃ ከምትገኘው
የአግሪት መንደር የኹለት ሰዓት የእግር ጉዞ ያስኬዳል። ደብሩ የሚገኝበት ስፍራ ደብረዳሪት ይባላል። ደብሩ የታነፀው በ1330ዎቹ
አቡነ አሮን በተባሉ የሐይማኖት አባት ነው። ገዳሙ በዋሻ ውስጥ ተፈልፍሎ የተሰራ ነው። ደብሩ ዐምስት የተለያዩ ክፍሎች
አሉት። በየክፍሎች አራት አራት አምዶች ይገኛሉ። ገዳሙ ኹለት በሮችና ሰባት መስኮቶች አሉት። የበሩ መግቢያ ባለኹለት
ተከፋች ነው። ከሰባቱ መስኮቶቹ አንደኛው በጣራው ላይ ይገኛል። የጣራው መስኮት መዝጊያ የሌለው በመሆኑ በፀሐይ ጊዜ
ብርሃን ያስገባል። በዝናብ ጊዜ ግን ምንም ውኃ አያስገባም። ይህንን ተዓምረኛ መስኮት ስቁረት በማለት ይጠሩታል።

ëëë እስካሁን ካዳመጣችሁት ታሪክ ምን ተረዳችሁ? ëëë

አቡነ አሮን ዋሻውን ለመፈልፈል የተጠቀሙበት መጥረቢያ በማህደር ሆኖ ተቀምጧል። ለገዳሙ አገልግሎት የሚሰጡ ኹለት
ሙቀጫዎች አሉ። የደብሩ ካህናት እንደሚሉት ከሙቀጫዎቹ አንደኛው ከእንቧጮ የተሰራ ነው። በርካታ ጥንታዊ ስዕሎችና
የብራና መጻሕፍት ይገኛሉ። የአቡነ አሮን መቃብርም በገዳሙ ውስጥ ይገኛል።
(ምንጭ፤ የአማራ ክልልና መስህቦቿ። ቀን የሌለው መጠነኛ ማሻሻያ ተደርጎ የተወሰደ)

44 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 5 ጉብኝት #4


ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎችን ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ረጋ ብለው በጥሩ አነባበብ ያንብቡላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ንባብዎን ገታ አድርገው ጥያቄውን
ይጠይቋቸው፤ መልሳቸውን ተቀብለው ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎች ታሪኩን መሠረት አድርገው በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ለተሰጡት ቃላት የመዝገበ ቃላት ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ። መዝገበቃላት ተጠቅመው ስለመዝገበ ቃላት አጠቃቀም መግለጫ
ይስጧቸው።)
[ተ. ለተሰጡት ቃላት የመዝገበቃላት ፍቺ ይሰጣሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. ለማንበብ የሚቸገሩ ተማሪዎችን ከጥሩ አንባቢ ተማሪዎች ጋር በማጣመር እየተጋገዙ “ካፒቴን ስለናት” የሚለውን ታሪክ
አቀላጥፈው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ከጓደኞቻቸው ጋር እየተጋገዙ አቀላጥፈው ያነባሉ።]

5.1.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “ጢስ አባይ ፏፏቴ” የሚለውን ታሪክ በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. “ጢስ አባይ ፏፏቴ” የሚለውን ታሪክ በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

45 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 5 ጉብኝት #5


ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡት ቃላት በምንባቡ ውስጥ ባላቸው ፍቺ ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ መመሪያ ይስጡ። በቅድሚያ ምሳሌ ያሳዩአቸው።)
[ተ. በቃላቱ ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

መጻፍ (10 ደቂቃ)


(መ. ስለጢስ አባይ ፏፏቴ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው ይጽፋሉ።]

5.1.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

ድኅረማዳመጥ (15 ደቂቃ)


(መ. “የአቡነ አሮን ገዳም” የሚለውን ታሪክ በድጋሚ ያንብቡላቸው። በመቀጠል የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ባዳመጡት ታሪክ
መሠረት በቃል እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንደአስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ታሪኩን በጥንቃቄ ያዳምጣሉ፤ ባዳመጡት ታሪክ መሠረት የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በቃል ይመልሳሉ፡፡።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ዓረፍተነገር በመስራት የቃላቱን አውዳዊ ፍቺ እንዲያሳዩ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
ምሳሌ፤ ሴትዮዋ የቡና ቁርስ መቁላት ስለፈለገች በቆሎ መፈልፈል ጀመረች።
[ተ. ቃላቱ አውዳዊ ፍቺ እንዲያሳዩ አድርገው ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (15 ደቂቃ)


(መ. ለማንበብ የሚቸገሩ ተማሪዎችን ከጥሩ አንባቢ ተማሪዎች ጋር በማጣመር እየተጋገዙ እንዲያነቡ “ካፒቴን ስለናት” የሚለውን
ታሪክ አቀላጥፈው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ከጓደኞቻቸው ጋር እየተጋገዙ አቀላጥፈው ያነባሉ።]

46 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 5 ጉብኝት #6


5.1.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በ “ሀ” ክፍል ላሉት ቃላት ከ “ለ” ክፍል ተመሳሳያቸውን እየመረጡ እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

መጻፍ (30 ደቂቃ)


(መ. የቱሪስት መስህቦች ለዜጎች የሚሰጡትን ጠቀሜታ በመዘርዘር ኹለት አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ። በቅድሚያ ለአስጎብኝዎች፣
ለሆቴሎች፣ ለአሽከርካሪዎች ወዘተ የሚሰጡትን ጠቀሜታ እንዲዘረዝሩ ያድርጉ። ከዚያም ባዘጋጁት ዝርዝር እየተመሩ
አንቀጾቹን እንዲጽፉ ያግዟቸው።)
[ተ. ኹለት አንቀጾች ይጽፋሉ።]

5.1.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. ከቀረቡት ቃላት ውስጥ ዋና ቃሉንና ቅጥያዎችን ለይተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)

[ተ. ዓመታት - ኣት]


[ተ. በራሪ -ዎች]
[ተ. ክልል -ኣችን]
(መ. በዓረፍተነገሮቹ ውስጥ ያሉትን ቅጽሎች ለይተው እንዲያመለክቱ ያድርጉ።)

[ተ. ጎበዝ] [ተ. ትልቅ ]


[ተ. ረጅም] [ተ. ብዙ]
(መ. ለተማሪዎች ስለቅጽል ምንነት ማብራሪያ ይስጧቸው፤)

ማስታወሻ
ቅጽሎች የስም ገላጮች ናቸው። የሚገልጹትም የስሙን አይነት፣ መጠንና ባህሪ ነው። በዚህም የስሙን ቀለም፣ መልክ፣ ቅርጽ፣
ባህሪ፣ ወዘተ ለማመልከት የሚያገለግሉ ናቸው።

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. ቅጽሎችን ተጠቅመው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጓቸው፤ እንዳስፈላጊነቱ ምሳሌ ሠርተው ያሳዩ። ተጨማሪ ተግባር
ሊሰጧቸው ይችላሉ።)
[ተ. ቅጽሎችን ተጠቅመው ዓረፍነገር ይመሠርታሉ።]

47 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 5 ጉብኝት #7


5.2.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) የጎዜ መስጊድ

የጎዜ መስጊድ

የጎዜ መስጊድ ከደብረብርሃን ከተማ 93 ኪሎሜትር ርቃ ከምትገኘው የሸዋሮቢት ከተማ በስተምዕራብ በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት
ላይ ይገኛል። የተሰራው በ15ኛ መቶ ክፍለዘመን ነው። ከ500 ዓመታት በላይ ዕድሜ እንዳለው ይነገርለታል። አሠራሩ አራት
ማዕዘን ነው። ግድግዳውና ጣራው ባልተጠረቡ ድንጋዮች ተገንብቷል። የድንጋዩን ክዳን የተሸከሙት አራት አግዳሚ የጣውላ
ወራጆች ናቸው። አራት ምሰሶዎችም አሉት። መስጊዱ የአርጎባን መንደሮች በስተግርጌው አድርጎ ከኮረብታ ላይ ይገኛል።
በዙሪያው ጥንታዊ የመቃብር ስፍራና የድሮ ኗሪዎች የዉኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓዶች አሉት። በውስጡ ደግሞ የሃይማኖቱ መሪዎች
አራት ጦሮች ይገኛሉ።

የአርጎባ ማኅበረሰብ አባላት በመስጊዱ ዙሪያ ይኖሩ ነበር። አሁን ግን ኮረብታውን ለቀው ከግርጌ መንደራቸውን መሥርተው
ይኖራሉ። ይሁን እንጅ መስጊዱ አሁንም ዋነኛ የእምነት ቦታቸው ነው። ይህ መስጊድ የአርጎባን ማኅበረሰብና በአካባቢው ያለውን
ውብ የተፈጥሮ መስህብ በስተግርጌው አድርጎ ሲታይ ዓይንን ይማርካል።
(ምንጭ፤ የአማራ ክልልና መስህቦቿ። ቀን የሌለው፤ መጠነኛ ማሻሻያ ተደርጎ የተወሰደ)

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. ታሪኩን ከማዳመጣቸው በፊት በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከተማሪዎች ጋር ይወያዩ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ከመምህር ጋር ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “የጎዜ መስጊድ” የሚለውን ታሪክ ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። እንዳስፈላጊነቱ ደግመው ያንብቡላቸው።)
[ተ. ታሪኩን በጥንቃቄ ያዳምጣሉ፤ መልዕክቱን ይረዳሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲሰሩ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (8 ደቂቃ)
መ. (ቃላቱን ከተቃራኒያቸው ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ማዕዘን- ቀጥ ያለ፣ ውብ- የማያምር፣ …በማለት ያዛምዳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (12 ደቂቃ)


መ. (“አይጠየፍ” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

48 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 5 ጉብኝት #8


5.2.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “ጣናን በጨረፍታ” የሚለውን ታሪክ ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ለየብቻቸው በለሆሳስ ያነባሉ። መልዕክቱንም ይገነዘባሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ያነባሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. በዓረፍተነገሮቹ ለተሰመረባቸው ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ።”)
[ተ. ሀ. አቋርጦ ለ. ፎቅ/ ከፍ ያለ ማማ ሐ. ውበት ... በስፋት ተኝቶ/ተንሰራፍቶ]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ ላይ ያሉትን መነሻ ሐሳቦች መሠረት በማድረግ ስለዘንገና ሐይቅ የተሟላ አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ዘንገና ሐይቅ በአማራ ክፍል በአዊ ብሔረሰብ ዞን ይገኛል። የሐይቁ መልክ ከሌሎች ሀይቆች በተለየ ሁኔታ አረንጓዴ ነው።
ዙሪያው በደን የተከበበ ሀይቅ ነው። ሀይቁ ለመዝናኛነት ስለሚያገለግል የተለያዩ ሰዎች በተለይ በዕረፍት ቀን ለመዝናናት
ወደሀይቁ ይሄዳሉ።]

5.2.3 ማዳመጥ (20 ደቂቃ)

የማዳመጥሂደት (7 ደቂቃ)
(መ. የጎዜ መስጊድ የሚለውን ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው”)
[ተ. ታሪኩ ሲነበብ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (13 ደቂቃ)


(መ. ባዳመጡት ታሪክ መሠረት የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

49 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 5 ጉብኝት #9


ቃላት (10 ደቂቃ)
(መ. በተሰጡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲያሳዩ አድርገው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጉ።)
[ተ. በቃላቱ ዓውዳዊ ፍቺ ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “አይጠየፍ” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

5.2.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ለቀረቡት ቃላትና ሐረጋት በታሪኩ መሠረት ተመሳሳይ ቃል እንዲፈልጉ ያድርጉ።)
[ተ. ለቃላቱና ለሐረጋቱ በታሪኩ መሠረት ተመሳሳይ ቃልና ሐረግ ይፈልጋሉ።]

መጻፍ (30 ደቂቃ)


(መ. ታሪካዊ ቦታዎችን መጎብኘት ስለሚያስገኘው ጠቀሜታ አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ። ትምህርታዊ ጠቀሜታ፣ የማዝናናት
ጠቀሜታ፣ ማህበራዊ ጠቀሜታ ወዘተ በማለት ሐሳባቸውን እያደራጁ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪካዊ ቦታን መጎብኘት ስለሚያስገኘው ጠቀሜታ አንቀጽ ይጽፋሉ።]

5.2.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በዓረፍተነገሮች ውስጥ ያሉትን ቅጽሎች ለይተው እንዲጽፉ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ቅጽሎችን ለይተው ይጽፋሉ።]

መጻፍ (30 ደቂቃ)


(መ. ጅምሩን አንቀጽ ሐሳብ በመጨመር አስፋፍተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ሐሳብ በመጨመር ጅምሩን አንቀጽ አስፋፍተው ይጽፋሉ።]
[ተ. የአማራ ክልል በርካታ የቱሪስት መስህቦች የሚገኙበት ክልል ነው። ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ከሆኑት የቱሪስት መዳረሻዎች
መካከል የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል። የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክና የጎንደር አብያተ መንግስታት ዋነኛ የቱሪስት
መዳረሻዎች ሲሆኑ በየዓመቱ ከውጪና ከሀገር ውስጥ በርካታ ጎብኝዎች ወደ ቦታው ይጎርፋሉ።
የላልይበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትም አለምን ያስደመሙ ጥንታዊ የኪነህንጻ ሥራዎች የሚታይባቸው የቱሪስት መዳረሻ
ቦታዎች ናቸው። በተጨማሪም ጢስ አባይ ፏፏቴንና ጣና ሀይቅን የመሳሰሉት ተፈጥሯዊ የቱሪስት ቦታዎች ክልሉ በቱሪስት
መስህብ የበለጸገ ለመሆኑ ማሳያዎች ናቸው።]

50 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 5 ጉብኝት $


5.3.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) ይስማ ንጉሥ

ይስማ ንጉሥ

በ1881 ዓ.ም. አጼምንሊክና የኢጣሊያ ተወካይ ኮን አንቶኔሊ የውጫሌን ውል የተፈራረሙበት ቦታ ይስማ ንጉሥ ይባላል። ይህ
ታሪካዊ ቦታ ከደሴ ወልድያ መንገድ 60 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ውጫሌ ከተማ ለመድረስ ሰባት ኪሎሜትር ሲቀር
ወደግራ ገባ ብሎ ከአንባሰል ተራራ ግርጌ ይገኛል። ቦታው ኢጣሊያ በውጫሌ ውል ስምምነት አማካይነት ኢትዮጵያን በቅኝ
ግዛት ለመያዝ ሴራ የሸረበችበት ነው። ይህ ሴራ በመጋለጡ በሀገራቱ መካከል ውዝግብ እንደተፈጠረና ለጥቁር ህዝቦች ነጻነት ፈር
ቀዳጅ የሆነው ታላቁ የአድዋ ጦርነት እንደተጀመረ ታሪክ ያስረዳል።

ëëë ቀጣዩ ታሪክ ስለምን ይመስላችኋል ëëë

የቦታው ስያሜ የተሰጠው የአፄ ምንሊክ ባለቤት በሆኑት በእቴጌ ጣይቱ ብጡል ነው። ስያሜው የውሉን 17ኛ አንቀጽ ለማፍረስ
በጊዜው የተገደዱበትን ታሪካው ገጽታ የሚያንጸባርቅ ነው። ከተናገሩትም “ይስሙ ንጉሥ! ጦርነት አልወድም ከዚህ መሳይ ውል
ግን ጦርነት እመርጣለሁ” የሚለው ይጠቀሳል። ከዚህ በመነሳትም ለቦታው ይስማ ንጉሥ የሚል መጠሪያ ተሰጥቶታል።

ከይስማ ንጉስ በቅርብ ርቀት ከሰሜን ወደደቡብ ተዘርግቶ ከሰማይ ጋር የገጠመ የሚመስለው ስመገናናው የአምባሰል ተራራም
ከነግርማ ሞገሱ ይታያል።
(ምንጭ፤ የአማራ ክልልና መስህቦቿ። (ቀን የሌለው)። መጠነኛ ማሻሻያ ተደርጎ የተወሰደ)

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ርስበርስ ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. የሚከተለውን ታሪክ ረጋ ብለው ያንብቡላቸው፤ እንዳስፈላጊነቱ ደግመው ሊያነቡ ይችላሉ። የማንበብ ሂደት ጥያቄ ላይ
ሲደርሱ ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ በጥሞና ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን መሠረት አድርገው የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. በ “ሀ” ክፍል ያሉትን ቃላት አብረዋቸው የሚሄዱ ቃላትን ከ‹‹ለ›› ክፍል መርጠው እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላትን አብሯቸው ከሚሄድ ቃል ጋር ያዛምዳሉ።]

51 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 5 ጉብኝት $1


አቀላጥፎ ማንበብ (15 ደቂቃ)
(መ. “ጉዛራ ቤተመንግስት” የሚለውን ታሪክ ከመምህር ጋር እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ
ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ከመምህር ጋር እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

5.3.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ በቀረቡት ቃላት ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ያደርጋሉ።]

ድኅረንባብ (15 ደቂቃ)


(መ. በታሪኩ መሠረት ሠንጠረዡን አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ። ስለአሠራሩ ማብራሪያ ይስጧቸው።)
[ተ. በታሪኩ መሠረት ሠንጠረዡን አሟልተው ይጽፋሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ሠንጠረዡን በደብተር ላይ በማስፈር በተሰጡት ቃላት በምንባቡ አውድና ከምንባቡ አውድ ውጪ ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ
ያድርጉ።)
[ተ. በቃላቱ ከምንባቡ አውድና ከምንባቡ አውድ ውጪ ባላቸው ፍቺ ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

መጻፍ (10 ደቂቃ)


(መ. ባዶ ቦታዎቹን በቅጽልና በግስ በማሟላት ዓረፍተነገሮች እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ብዙ ጓደኞች አሉኝ] [ተ. አዲስ መጽሐፍ ሰጠኝ]
[ተ . ቀይ ሸሚዝ ለበሰ] [ተ. ሰፊ ቤት ገዛ]

5.3.3 ማዳመጥ (20 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “ይስማ ንጉሥ” የሚለውን ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው።)
[ተ. ታሪኩን ደግመው ያዳምጣሉ። ዋናውን ሐሳብ ይገነዘባሉ።]

ድኅረማዳመጥ (13 ደቂቃ)


(መ. በታሪኩ መሠረት የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

52 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 5 ጉብኝት $2


ቃላት (8 ደቂቃ)
(መ. በ “ሀ” ክፍል ለቀረቡት ቃላት ከ “ለ” ክፍል ተመሳሳያቸውን በመምረጥ እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (12 ደቂቃ)


(መ. “ጉዛራ ቤተመንግስት” የሚለውን ታሪኩ ከጓደኞቻቸው ጋር እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ
በማድረግ አቀላጥፎ ማንበብን ያለማምዱ።)
[ተ. ታሪኩን ከጓደኞቻቸው ጋር እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ በማንበብ ይለማመዳሉ።]

5.3.4 መጻፍ (40 ደቂቃ)

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. መዝገበ ቃላት ተጠቅመው ለቃላት ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ።)
[ተ. ለቃላቱ የመዝገበቃላት ፍቺ ይሰጣሉ።]

መጻፍ (30 ደቂቃ)


(መ. ጅምሩን ሐሳብ በተገቢ ሐሳብ በማሟላት አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ጅምሩን ሐሳብ በተገቢ ሐሳብ በማሟላት አንቀጽ ይጽፋሉ።]

5.3.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (20 ደቂቃ)


(መ. ቅጥያዎቹን ከተገቢ ቃል ጋር በማዛመድ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ሰሜን -ኣዊ = ሰሜናዊ] [ተ. ማረፍ -ኢያ = ማረፊያ]
[ተ. ግንብ -ኧኛ = ግንበኛ] [ተ. ነገሥት -ኣት = ነገሥታት]
(መ. ከቀረቡት ቃላት ጋር ተመሳሳይ ፍቺ ያላቸው ቃላት ከታሪኩ ፈልገው እንዲያወጡ ያድርጉ።)
[ተ. ለቃላት ተመሳሳይ ፍቺ ከታሪኩ ውስጥ ፈልገው ያወጣሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. ቅጽሎችን ተጠቅመው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ተጨማሪ ተግባር ይስጧቸው።)
[ተ. መምህራችን ሰነፍ ተማሪ አይወዱም።
ብልህ ሰው ከሌሎች ለመማር ዝግጁ ነው።]

53 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 5 ጉብኝት $3


ምዕራፍ ስፖርት
6

የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
ƒƒ ተመሳሳይ መረጃዎችን አዳምጠው መልዕክቶቹን በቃል ይለዋወጣሉ፤
ƒƒ በእያንዳንዱ አንቀፅ ውስጥ የሚገኘውን ጽሑፍ ሐሳብ አንብበው ያብራራሉ፤
ƒƒ የቃላት እውቀታቸውን በልምምድ ያሳድጋሉ፤
ƒƒ የባለቤትና ማሰሪያ አንቀፅ ስምምነት ያላቸውን ዓረፍተነገሮች ይመሠርታሉ።

6.1.1 ማዳመጥ (25 ደቂቃ) ዘመናዊ ስፖርትና ደጋፊዎቹ

ዘመናዊ ስፖርትና ደጋፊዎቹ

ዘመናዊ ስፖርት ዘመናዊ የውድድር ቦታ ተዘጋጅቶለት በብዙ ተመልካቾች ታጅቦ ይከናወናል። ዘመናዊ ስፖርት በዓይነት እየበዛና
በክንውኑም በጣም አስደሳች እየሆነ መጥቷል። ይህን የስፖርት አይነት በሦስት ከፍሎ ማየት ይቻላል።
አንደኛው የኳስ ጨዋታ ሲሆን የእግር ኳስ፣ የመረብ ኳስ፣ የቅርጫት ኳስ፣ የጠረጴዛ ኳስና የእጅ ኳስ ተብሎ ይከፈላል። እነዚህ የኳስ
ጨዋታ ዓይነቶች በቡድን አንዳንዴም በጥንድ የሚከናወኑ ናቸው። ለምሳሌ የእግር ኳስና የመረብ ኳስ በቡድን፣ የጠረጴዛ ኳስ ደግሞ
በጥንድ የሚከናወኑ ናቸው።
ኹለተኛው ዘመናዊ ስፖርት “ሩውዝ” ወይም አትሌቲክስ ነው። ከስያሜው እንደምንረዳው ይህ ዘርፍ ሩጫን፣ ውርወራንና ዝላይን
ያካትታል። ሩጫ በተለያዩ ርቀቶች ከትምህርትቤት ጀምሮ እስከዓለምአቀፍ የሚከናወን ነው። አገራችን ኢትዮጵያ በሩጫ ውድድር
ዓለምአቀፍ እውቅና አላት።
ሶስተኛው የአካል ብቃት እንቅስቃሴን፣ ክብደት ማንሳትንና ሌሎችን ያካትታል። ከጨዋታዎች ባህሪ አንጻር ከከተማ እስከገጠር
ታዋቂነት ባይኖራቸውም የቦክስ፣ የሜዳ ቴኒስና የጎልፍ ስፖርቶችም ዘመናዊ ናቸው። ከእነዚህ ሁሉ በተጨማሪ ዘመናዊ ስፖርት
በመኪና በሞተር ሳይክልና በተራ ባይስክል የሚደረጉ ውድድሮችንም ያካትታል።
ዘመናዊ ስፖርት ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ነው። ተጫዋቾቹ ብዙ ገንዘብ እየተከፈላቸው ለአንድ ቡድን ሲሰለፉ ማየት የተለመደ
ሆኗል። ተመልካቾች ገንዘብ ከፍለው ስታዲየም በመግባት ጨዋታውን መመልከት ያስደስታቸዋል። አንዳንድ ሰዎች ጨዋታውን
ከሚታደሙት ሰዎች በሚሰበሰበው ገንዘብ የዓለም ቱጃር ለመሆን በቅተዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ጨዋታውን በቴሌቪዝን
ለሚመለከቱ ግለሰቦች የውርርድ ትኬቶችንም በመሸጥ ገቢ የሚሰበስቡ ድርጅቶችም እየበዙ መጥተዋል። በዚህ የተነሳ የኳስ ጨዋታ
በተለይ የእግር ኳስ ጨዋታ የቁማርተኞች መፈልፈያ እየሆነ ነው።
(ምንጭ፡- አራተኛ ክፍል አማርኛ እንደአፍመፍቻ ቋንቋ የመምህር መምሪያ (2006) ተሻሽሎ የተወሰደ።)

54 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት $4


ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ፤ መልስና ማብራሪያ አይስጡ፤ ራሳቸው ግምታቸውን በማዳመጥ ሂደት
ያረጋግጣሉ። ለማዳመጥ ዝግጁ ያድርጓቸው።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. “ዘመናዊ ስፖርትና ደጋፊዎቹ” የሚለውን ታሪክ ረጋ ብለው ያንብቡላቸው፤ እንዳስፈላጊነቱ ደግመው ሊያነቡ ይችላሉ።
የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. ታሪኩን መምህር ሲያነቡ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ። መልሳቸውን ለመምህር ያሳያሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. ለተሰመረባቸው ቃላት ከታሪኩ ውስጥ ተመሳሳያቸውን ፈልገው እንዲተኩ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ቃላቱ የሚገኙበትን
አንቀጽ ሊጠቁሟቸው ይችላሉ።)
[ተ. ቃላቱን በተመሳሳይ ቃል ይተካሉ።]
[ሀ. ዘግይቶ ለ. በጋራ ሐ. ተፎካካሪ መ. ለስያሜው]

6.1.2 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
(መ. ታሪኩን ከማንበባቸው በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ያደርጋሉ።]

የማንበብ ሂደት (5 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን በየግላቸው በለሆሳስ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. በታሪኩ መሠረት የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን እንዲያሟሉ ያድርጉ፤ ቀድመው ለሚጨርሱ ጎበዝ ተማሪዎች ተጨማሪ ጥያቄ
እንዲሰሩ ይጠይቋቸው።)
[ተ. በታሪኩ መሠረት የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው ይጽፋሉ።]

55 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት $5


ቃላት (10 ደቂቃ)
(መ. ከቃላት ውስጥ ዋና ቃልንና ቅጥያዎችን ለይተው እንዲጽፉ ያድርጉ። ምሳሌ ሠርተው ያሳዩ፤ ግብረመልስም ይስጧቸው።)
ለምሳሌ፡-

[ተ. ጀግኖቻችን = ዋና ቃል = ጀግና ፤ ቅጥያዎች = -ኦች ፣ -ኣችን


ዘመናዊ = ዋና ቃል = ዘመን ቅጥያ = -ኣዊ]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን ቃላት በምንባቡ ውስጥ ያላቸውን ፍቺ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱ በምንባቡ ውስጥ ያላቸውን ፍቺ ይጽፋሉ።]

6.1.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ)


(መ. “ስፖርት” የሚለውን ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው።)
[ተ. ታሪኩን ደግመው ያዳምጣሉ። ለመረዳት ማስታወሻ ይጽፋሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ያዳመጡትን ታሪክ መሠረት አድርገው ጥያቄዎቹን በቃል እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ታሪኩን መሠረት አድርገው ጥያቄዎቹን በቃል ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ስፖርት” የሚለውን ታሪክ አንቀጽ እየተቀባበሉ በትክክል በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. የታሪኩን አንቀጾች በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. ስለገበጣ አጨዋወት ህግ አጭር አንቀጽ ጽፈው በክፍል ውስጥ እንዲያነቡ ያድርጉ። ገበጣ የማያውቁ ከሆነ ሌላ የጨዋታ
አይነት መርጠው ሊጽፉ ይችላሉ።)
[ተ. ስለገበጣ አጨዋወት አጭር አንቀጽ ጽፈው በክፍል ውስጥ ያነባሉ።]

6.1.4 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው ያስነብቡ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት በየግላቸው በለሆሳስ ያነባሉ።]

56 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት $6


ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. ታሪኩን መሠረት አድርገው የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በቃላቸው ይመልሳሉ።]

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር እንዲሰሩ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ዓረፍተነገር በመስራት
ያሳዩ።)
[ተ. ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. አያያዥ ቃላትን በተገቢ ቦታቸው በማስገባት አንቀጹን አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ
ይስጧቸው።)
[ተ. አያያዥ ቃላትን በተገቢ ቦታቸው በማስገባት አንቀጹን አሟልተው ይጽፋሉ።]

6.1.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (20 ደቂቃ)


መ. (ባህላዊ ስፖርት ከዘመናዊ ስፖርት የበለጠ ሰዎችን ያዝናናል የሚለውን ሐሳብ በመደገፍ ወይም በመቃወም ተማሪዎች
እንዲከራከሩ ያድርጉ። ስለክርክር የአቀራረብ መመሪያ ለተማሪዎች ይንገሯቸው።)
ተ. [ባህላዊ ስፖርት ከዘመናዊ ስፖርት የበለጠ ሰዎችን ያዝናናል የሚለውን ሐሳብ በመደገፍ ወይም በመቃወም ይከራከራሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን ሥርዐተነጥቦች በዓረፍተነገሮቹ ውስጥ በተገቢ ቦታ አስገብተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ.] ለምሳሌ፡- [ሩጫ፣ ውርወራና ዝላይ የአትሌቲክስ ስፖርቶች ናቸው።]
[ከባህላዊ ስፖርት የምትወደው የቱን ነው?]
[እግርኳስ መመልከት እወዳለሁ ፤ ነገርግን መጫወት አልችልም።]
[መምህሯ፡- “ስምሽ ማነው?” ብላ ጠየቀች።]

57 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት $7


6.2.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) ስፖርት

ስፖርት ለጤንነት
ሰው በአካሉ ገዝፎ እንዳያጣ ጤና፣
ጥንካሬን አጥቶ ሰርቶ እንዳይዝናና፣
በሽተኛ እንዳይሆን ታስሮ በስንፍና፣
ስፖርት ጠቃሚ ነው ለሰው ህልውና።
ያለልክ መጠጣት እንዳገኙ መብላት፣
ስራን ቸል ብሎ እንደልብ መተኛት፣
ጤናን ያጎድላሉ ያመጣሉ ጉዳት፣
ለእኒህ ሁሉ ጠንቆች መድሃኒት ነው ስፖርት።
ስፖርት ለጤንነት በእጅጉ ይጠቅማል፣
ለአካል ጥንካሬም በጣም ያስፈልጋል፣
ጠንካራ ድልድይ ነው ሁሉን ያገናኛል፣
በፍቅር አስተሳስሮ አንድነት ይፈጥራል።
ደስተኛ እንዲሆን አካሉ በርትቶ፣
ጤናው ተጠብቆ ህሊናው ረክቶ፣
ስራውን ከውኖ ሂወቱ እንዲሰምር፣
ልጅ አዋቂ ሳይል ስፖርትን ያዘውትር።

ቅድመማዳመጥ (2 ደቂቃ)
(መ. በቀረቡት ጥያቄዎች ላይ ከመምህር ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. የሚከተለውን ግጥም በግጥም አነባበብ ስልት ያንብቡላቸው፤ እንዳስፈላጊነቱ ደግመው ሊያነቡ ይችላሉ።)
[ተ. መምህር ግጥሙን ሲያነቡ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (8 ደቂቃ)
(መ. ባዳመጡት ግጥም መሠረት ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

58 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት $8


የቃላት አጠቃቀም (20 ደቂቃ)
(መ. በተሰጡት ቃላትና ሐረጋት አውዳዊ ፍቺ እንዲያሳዩ አድርገው ዓረፍተነገር እንዲጽፉ ይዘዟቸው። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ
ይስጧቸው።)
[ተ. በቃላትና በሐረጋት አውዳዊ ፍቺ እንዲያሳዩ አድርገው ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]

6.2.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “ስፖርትና ጥቅሙ” የሚለውን ምንባብ በለሆሳስ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ምንባቡን በየግላቸው ለመረዳት ያነባሉ። ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. የአንቀጾቹን ዋና ሐሳብ በመጻፍ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን እንዲያሟሉ መመሪያ ይስጡ። የየአንቀጾችን ሐሳብ በትክክል
መጻፋቸውን ያረጋግጡ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የአንቀጾቹን ዋና ሐሳብ በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ ላይ ይጽፋሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ዋና ቃሉንና ቅጥያዎቹን ለያይተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ዋና ቃሉንና ቅጥያዎቹን ለያይተው ይጽፋሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. ለቃላቱና ሐረጋቱ አውዳዊ ፍቺ እንዲጽፉ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ለቃላቱና ለሐረጋቱ አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ።]
ምሳሌ፡- [መ. የስራ መስክ - የሙያ ዘርፍ]
(መ. ለተሰጡት ቃላት የመዝገበ ቃላት ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ። መዝገበ ቃላት ሊያቀርቡላቸው ይገባል፤ ስለአጠቃቀሙ ማብራሪያ
ይስጡ።)
[ተ. ለቃላቱ የመዝገበቃላት ፍቺ ይሰጣሉ።]

59 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት $9


6.2.3 ማዳመጥ (10 ደቂቃ)

(መ. “ስፖርት ለጤንነት” የሚለውን ግጥም በድጋሚ ያንብቡላቸው ፤ በመቀጠል በግጥሙ መሠረት የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን
እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የግጥሙን ታሪክ መምህር በድጋሚ ሲያነቡ በጥሞና አዳምጠው የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ስፖርትና ጥቅሙ” የሚለውን ታሪክ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ በቡድን እየተቀባበሉ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ በቡድን እየተቀባበሉ ያነባሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. ጅምር ስንኞችን በራሳቸው ሐሳብ አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. የተጓደሉ ስንኞችን አሟልተው ይጽፋሉ።]

6.2.4 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ምንባቡን ለመረዳት ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው እንዲያነቡ ያድርጉ። ሁሉም ተማሪዎች ማንበባቸውን ያረጋግጡ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (13 ደቂቃ)


(መ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በታሪኩ መሠረት እንዲያሟሉ ያድርጉ።)
[ተ. ለኩላሊት፣ ለልብ፣ ለጡንቻ ፣ ለአዕምሮ .. የሚሰጠውን ጠቀሜታ ይገልጻሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ዋና ቃልና ቅጥያዎቹን አጣምረው ቃል እንዲመሠርቱ ያድርጉ። ምሳሌ ያሳዩአቸው፤ ግብረመልስም ይስጧቸው።)
ምሳሌ፡- [አዕምሮ - ኣቸው - ን= አዕምሯቸውን]
[ተ. ዋናውን ቃልና ቅጥያዎቹን አገጣጥመው ቃል ይመሠርታሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. መሸጋገሪያ ቃላቱንና ሐረጋቱን በመጠቀም አንቀጹን እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. መሸጋገሪያ ቃላቱንና ሐረጋቱን ተጠቅመው አንቀጹን አሟልተው ይጽፋሉ።]

60 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት %


6.2.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (25 ደቂቃ)


(መ. “በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች ላይ መሳተፍ የትምህርት ጊዜን ይሻማል” የሚለውን ሐሳብ በመደገፍ ወይም በመቃወም በቡድን
እንዲከራከሩ ያድርጉ። ተማሪዎች ሐሳባቸውን ያለፍርሃት እንዲናገሩ ያበረታቷቸው።)
[ተ. በተሰጠው መንደርደሪያ ሐሳብ ላይ ክርክር ያደርጋሉ።]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. ተስማሚ ሥርዓተነጥብ በማስገባት ዓረፍተነገሮቹን እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ። ስለሥርዓተነጥቦች አገልግሎት ማብራሪያ
ይስጧቸው።)
[ተ. ሥርዓተነጥቦቹን በማስገባት በትክክል ይጽፋሉ። [መ. ወይኔ አደፍርስ! “አፍንጫህን ላስ” አለኝ እኮ!]
(መ. ገና አራተኛ ክፍል ነው፤ ነገርግን በርካታ መጻሕፍት አንብቧል።)

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ


6.3.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ)
ጠቀሜታዎች
የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጠቀሜታዎች

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ ከአካል ብቃት መጎልበት ባለፈ በርካታ የጤና ጠቀሜታዎች እንዳሉት ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ሩጫ፣ የእግር ጉዞ፣ ዋና፣ ክብደት ማንሳትን ጨምሮ ልዩልዩ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ማድረግ የሚከተሉትን የጤና
ጠቀሜታዎች ያስገኛል።

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ሰውነት የጭንቀትና የድብርት ስሜትን ለማስወገድ የሚያግዘውን ሆርሞን እንዲያመነጭ ይረዳዋል።
የዚህ ሆርሞን መኖር ደግሞ የደስተኝነት ስሜትና ቀና አስተሳሰብ እንዲኖር ያደርጋል። የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጡንቻዎችን
ለማፈርጠም፣ አጥንትን ለማጠንከርና አቅምን ለማሳደግ ያስችላል። ባለሙያዎች እንደሚሉት ለስድስት ተከታታይ ሳምንት
የሚሰራ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ሰዎች በከፍተኛ ድካም እንዳይጠቁ ያደርጋል።

ëëë እስካሁን ካዳመጣችሁት ምን ተረዳችሁ? ëëë

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግ በበሽታ የመያዝ እድልን እንደሚጨምር ባለሙያዎች ይገልጻሉ። የአካል ብቃት እንቅስቃሴ
በደም ውስጥ ያለውን የስብ ክምችት እንዲሟሟ በማድረግ ለደም ግፊት የመጋለጥ እድልን እንደሚቀንስ ያስረዳሉ። አዘውትሮ
የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ ወደ አንጎል የሚሄደውን የደም ፍሰት በማስተካከል ለአዕምሮ ጤና ደህንነት ይረዳል። ከዚህ
ባለፈም ለአዕምሮ እድገት የሚረዱ ሆርሞኖችን በማመንጨት ለጤናማ የአዕምሮ እድገትና የማስታወስ ችሎታን ለማዳበር
ይጠቅማል።

በመደበኛነት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ በራስ የመተማመን ስሜት ለማዳበር እንደሚረዳ ባለሙያዎቹ ያስረዳሉ። ይህም
ሰውነት በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ወቅት አዎንታዊ አስተሳሰብ እንዲዳብር የሚረዱ አዳዲስ ህዋሶችን ከማመንጨቱ ጋር የተያያዘ
መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ምንጭ፦ healthline.com

61 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት %1


ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ምንባቡን ኹለት ጊዜ ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። የማዳመጥሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ማንበብዎን ለአፍታ ያህል ገታ አድርገው
ጥያቄውን ይጠይቁ፤ መልሳቸውን ካዳመጡ በኋላ ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ፤ ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ስለአካልብቃት እንቅስቃሴ ጠቀሜታዎች የተረዱትን ሐሳብ በሐሳብ ማደራጃ ቢጋር ላይ እንዲጽፉ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ
ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን ያሟላሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (20 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላት በፍቺ የተለያዩ ዓረፍተነገሮችን በመስራት የቃላቱን የተለያየ ፍቺ እንዲያሳዩ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱ የተለያየ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]

6.3.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመ ንባብ (2 ደቂቃ)


(መ. በቅድመንባብ ጥያቄ ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (8 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ለመረዳት በለሆሳስ እንዲያነቡ ያድርጉ። ማንበባቸውን ይከታተሉ።)
[ተ. ታሪኩን ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው ያነባሉ። ዋናውን ሐሳብ ለይተው ይረዳሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን ጥያቄዎች በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)

62 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት %2


ቃላት (10 ደቂቃ)
መ. (ከቃላት ውስጥ ቅጥያዎቹን ብቻ እንዲያወጡ ያድርጉ፤ ምሳሌ ሠርተው ያሳዩ።)
[ተ. አላገኘሁም አል- -ሁ -ም
[ተ. ልብሳችንን -ኣችን ን]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን ቃላት ከተመሳሳያቸው ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳይ ፍቻቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

6.3.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጠቀሜታዎች” የሚለውን ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (8 ደቂቃ)
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ። ግብረመልስ ይስጧቸው)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በቃላቸው ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “የስፖርት ክፍለ ጊዜያችን” ከሚለው ታሪክ አንድ አንቀጽ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ
እንዲያነቡ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ አንድ አንቀጽ በማንበብ አርዓያ ሆነው ሊያሳዩአቸው ይችላሉ።)
[ተ. የታሪኩን አንድ አንቀጽ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. “የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጠቀሜታዎች” የሚለውን ምንባብ አንቀጾች ሐሳብ በአራት ዓረፍተነገሮች አሳጥረው እንዲጽፉ
ያድርጉ።)
[ተ. የየአንቀጾቹን ዋና ሐሳብ አሳጥረው ይጽፋሉ።]

6.3.4 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “የስፖርት ክፍለጊዜያችን” የሚለውን ታሪክ ድምጽ ሳያሰሙ ደግመው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንቃቄ ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

63 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት %3


ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ። ለመልሳቸው ማብራሪያ በመጠየቅ የንግግር ክሂላቸው እንዲዳብር
ያድርጉ።)
[ተ. የድህረማንበብ ጥያቄዎቹን በቃላቸው ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. አብረው የሚሄዱ ቃላትን እየመረጡ እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ግብ ጠባቂ ፣ የስፖርት ትጥቅ ፣ የደንብ ልብስ፣ የፊሽካ ድምጽ]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር እንዲሰሩ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱ አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

6.3.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. መነሻና መድረሻ ቅጥያዎችን ከቃሉ ጋር በማጣመር አዲስ ቃል እንዲመሠርቱ ያድርጉ።)
[ተ. መነሻና መድረሻ ቅጥያዎችን ከቃላቱ ፊትና ኋላ ቀጥለው አዲስ ቃል ይመሠርታሉ። አስገመተች፤ ተለጋች፤ ተረዷቸው]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


መ. (ጅምር አንቀጹን በራሳቸው ሐሳብ አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።በሚከተለው መልኩ ሊጽፉ እንደሚችሉ ይጠበቃል።)
[ተ. የዛሬው ክፍለጊዜ የሩጫ ውድድር ነው። ከሦስት ክፍሎች ከአንድ እስከ አራት የወጣን ልጆች ዛሬ በሩጫ መም ላይ ተገናኝተናል።
እኔ ከዳር በኩል ተሰልፌኣለሁ። መምህራችን በመስመሩ ላይ በትክክል መቆማችንን አረጋገጡ። መምህራችን በቦታ! ሲሉ
ሁላችንም ወደመሬት በእጃችንና በአንድ ጉልበታችን ተንበረከክን። ጆሯችንን አቁመን ሂድ! የምትለዋን የመጨረሻዋ ድምጽ
እየጠበቅን ነው። ልቤ እየመታ ነው። መምህሩ “በቃ ሩጫው ቀርቷል” ሲሉን አንጀታችን ብጥስ አለ።]

64 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 6 ስፖርት %4


ምዕራፍ ዉኃ
7

የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
ƒƒ መደበኛ ባልሆነ መቼት ውስጥ በሚቀርብ ሚና ጨዋታ ድርሻ ወስደው ይጫወታሉ፤
ƒƒ የጽሁፉን ሐሳብ በዝርዝር አንብበው ያብራራሉ፤
ƒƒ የተሟላ አረፍተነገር በራስ ይፅፋሉ፤
ƒƒ ተውሳከ ግሶችን ተጠቅመው ዐረፍተነገሮችን ይመሠርታሉ፤
ƒƒ ስለውኃ የሚያትቱ መዝሙሮችን ይዘምራሉ፤
ƒƒ በተሰጣቸው ርዕሰጉዳይ ላይ ይከራከራሉ፤
ƒƒ የተሰጧቸውን ግሶች ተጠቅመው የተሟላ አረፍተነገር ይፅፋሉ።

7.1.1 ማዳመጥ (25 ደቂቃ) የዉኃ ህክምና

የዉኃ ህክምና

ዉኃ በፈሳሽ፣ በበረዶና በጋዝ መልኩ የተለያዩ ጠቀሜታዎችን ይሰጣል። ቀዝቃዛ፣ ሙቅና ፍል ዉኃም አገልግሎቱ ለየቅል ነው። ዉኃን
መጠጣት የሰውነታችንን በሽታ የመከላከል አቅምን  ያሳድጋል። ለምሳሌ ዉኃ በመጠጣት የኩላሊት፣ የጨጓራ፣ የፊኛ፣ የአንጀትና
የጣፊያ በሽታዎችን ወዘተ ማስወገድ ይቻላል።

ሁልጊዜ ጠዋት ቁርስ ከመመገባችን በፊት ከዐምስት ብርጭቆ ያላነሰ ዉኃ ብንጠጣ ለተለያዩ ውስጣዊ የጤና ችግሮቻችን መፍትሄ
እናገኛለን። ዉኃ በተፈጥሮው የአሲድነት ፀባይ የሌለው በመሆኑ ለሰውነታችን ውስጣዊ ኡደት መቀላጠፍ የሚሰጠው ጠቀሜታ
ከፍተኛ ነው። በአግባቡ ሳይታኘኩ ወደ አንጀታችን የሚገቡ ምግቦች በቀላሉ እንዲብላሉና በጥቅም ላይ እንዲውሉ በማድረግ ረገድ
ዉኃ የሚሰጠው ጠቀሜታ ከፍተኛ ነው።

በጣም የቀዘቀዘ ዉኃ ማይግሪን ለተባለው ራስ ምታት ፍቱን መድኀኒት ነው። ህመሙ በሚነሳበት ወቅት በጣም የቀዘቀዘ ዉኃን
ለዐምስት ደቂቃዎች ያህል አናት ላይ በመያዝ ህመሙን ማስታገስ ይቻላል። ቀዝቃዛ ዉኃ ለሌሎችም በሽታዎች ፍቱን መድኀኒት
ነው።

65 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ %5


ëëë ፍል ዉኃ ምን ምን ህመሞችን የሚፈውስ ይመስላችኋል? ëëë

ዉኃ በሞቃትና በፍል መልኩ ጥቅም ላይ ሲውል ደግሞ ለመገጣጠሚያ ችግሮች፣ ለጉንፋን፣ ለብርድ፣ ለኢንፍሉዌንዛ ፈዋሽ መድኀኒት
ነው። ሞቅ ያለ ዉኃ ህመም በሚሰማን ቦታ ላይ ማፍሰስ (መነከር) ከህመም እፎይታን ሊያስገኝ ይችላል። በአደጋ (መውደቅ፣
መጋጨት) በሚደርስ ጉዳት ሳቢያ በሰውነታችን ላይ ለሚከሰት እብጠት፣ የጡንቻ መሸማቀቅ ወይም ውልቃት በረዶ ፈጣን ፈውስን
ያስገኛል።

በዉኃ ህክምና በመታገዝ ፈውስ ለማግኘት በምንሞክርበት ወቅት ያሉብንን የጤና ችግሮች በሚያባብስ መልኩ እንዳይሆንብን
ልንጠነቀቅ ይገባል። ቁስለት ባለባቸው የሰውነት አካላት ላይ ሙቅም ሆነ ቀዝቃዛ ዉኃ መጠቀም የለብንም። ስለሆነም በዉኃ ህክምና
ፈውስ ለማግኘት ስናስብ የጤና ባለሙያዎችን ማማከር ጠቃሚ ነው።

ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ከማዳመጣቸው በፊት በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ርስበርሳቸው ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. “የዉኃ ህክምና” የሚለውን ምንባብ ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። እንዳስፈላጊነቱ ይድገሙላቸው። ድኅረማዳመጥ ጥያቄ ላይ
ሲደርሱ ማንበብዎን ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. ዋና ሐሳቡን እየተረዱ ታሪኩን በጥሞና ያዳምጣሉ፤ የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ይመልሳሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ባዳመጡት ምንባብ መሠረት የውኃ አይነቶችን ከፈውስ አይነቶች ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ይሠራሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላት አውድ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. በቃላቱ አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

7.1.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ርስበርስ እንዲወያዩና ዳራዊ እውቀታቸውን እንዲናገሩ ያድርጉ።)
[ተ. የቅድመንባብ ጥያቄዎቹን ተወያይተው ይመልሳሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን በለሆሳስ እንዲያነቡ ያድርጉ። ሁሉም ተማሪዎች ስለማንበባቸው ይከታተሉ።)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ፤ መልዕክቱን ይገነዘባሉ።]

66 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ %6


ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲሰሩ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ፡፡ ለምሳሌ በእጅ ያለ ነገር ውድነቱ አይታወቅም፤ ሁላችንም ዉሃ ስለምናገኝ
ለዉኃ የምናደርገው ጥንቃቄ አነስተኛ ነው።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በዓረፍተነገሮቹ የተሰመረባቸውን ቃላትና ሐረጋት ከሳጥኑ ውስጥ ተመሳሳያቸውን እየመረጡ እንዲተኩ ያድርጉ፤ ምሳሌ
ሠርተው ያሳዩ።)
[ተ. የተሰመረባቸውን ቃላትና ሐረጋት በተመሳሳይ ቃልና ሐረግ ይተካሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. ለተሰመረባቸው ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላት አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ።]

7.1.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ምንባቡን ደግመው ያንብቡላቸው። ሁሉም ተማሪዎች እያዳመጡ መሆናቸውን ያረጋግጡ።)
[ተ. የማዳመጥ ታሪኩ ሲነበብላቸው በጥሞና ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (8 ደቂቃ)
(መ. ጥያቄዎቹን ባዳመጡት ምንባብ “እውነት” ወይም “ሀሰት” ብለው በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ፤ ለምን እውነት ለምን ሀሰት
እንዳሉ ለመልሳቸው ማብራሪያ እንዲያቀርቡ ይጠይቋቸው።)
[ተ. የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎቹን በቃላቸው እውነት ወይም ሀሰት ብለው በምክንያት ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10ደቂቃ)


(መ. “በእጅ የያዙት ወርቅ” የሚለውን ታሪክ በህብረት አቀላጥፈው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. “በእጅ የያዙት ወርቅ” የሚለውን ታሪክ በህብረት አቀላጥፈው ያነባሉ።]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. የቀረቡላቸውን መነሻ ሐሳቦች በመጠቀም የተሟላ አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ)
[ተ. በመነሻ ሐሳቡ መሠረት የተሟላ አንቀፅ ይጽፋሉ።]

67 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ %7


7.1.4 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (8 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ደግመው እንዲያነቡ ያድርጉ። ሁሉም ተማሪዎች ማንበባቸውን ያረጋግጡ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት ደጋግመው በየግላቸው ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (12 ደቂቃ)


(መ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በታሪኩ መሠረት እንዲያሟሉ ያድርጉ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በታሪኩ መሠረት ያሟላሉ።]

መፍትሔ
መንስኤ ችግር
ƒƒ ሊመታው ብሎ ራርቶ ተወው፣
ƒƒ የልጁ ዉሃ መርጨት ƒƒ የአባትዬው መናደድ፤ መበሳጨት
ልጅም ይቅርታ ጠየቀ።

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ዋናውን ቃል ከቅጥያዎቹ ጋር አንድ ላይ አጣምረው አዲስ ቃል እንዲመሠርቱ ያድርጉ።)
[ተ. ሀ. ጠቀሜታዎችን ለ. መገጣጠሚያ ሐ. እንዳልሆነ]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. የተሰመረባቸውን ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲጽፉ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላት አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ።]

7.1.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (10 ደቂቃ)


(መ. “ለዉኃ ያለን ክብር ከሚሰጠን ጠቀሜታ አንጻር አነስተኛ ነው” የሚውን ሐሳብ በማስረጃ እንዲያብራሩ ያድርጉ።)
[ተ. በተሰጠው ርዕስ ላይ ሐሳባቸውን በማስረጃ እያቀረቡ ይናገራሉ።]

መጻፍ (30 ደቂቃ)


(መ. ዉኃንና ለስላሳ መጠጦችን በማወዳደርና በማነጻጸር ኹለት አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ፤ ለምሳሌ ዉኃናን ሚሪንዳን
አወዳድረውና አነፃፅረው ሊጽፉ ይችላሉ። የመጻፍ ሂደቱ ቀላል እንዲሆንላቸው በቅድሚያ በሁለቱ ነገሮች መካከል ያለውን
አንድነትና ልዩነት እንዲዘረዝሩ ያድርጉ። ከዚያም ያነሷቸውን ነጥቦች በማስፋፋት እንዲጽፉ ያድርጉ። በመጀመሪያ ግን
ሎሚንና ብርቱካንን በማነፃፀርና በማወዳደር ርስዎ ጽፈው አርአያ ሆነው ያሳዩኣቸው።)
[ተ. በማወዳደርና በማነጻጸር ኹለት አንቀጽ ይጽፋሉ።]

68 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ %8


7.2.1 ማዳመጥ (25 ደቂቃ) ዉኃና ጥቅሙ

ዉኃና ጥቅሙ

ህይወት ያለው ፍጡር ሁሉ ለመኖሩ ከሚያስፈልጉት ነገሮች መካከል አየርና ዉኃ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛሉ። እፅዋትና እንሰሳት
ያለ ዉኃ መቆየት አይችሉም። ለዚህም ነው “ዉኃ ህይወት ነው” የሚባለው።

ዉኃ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት። ከሰውነታችን ክብደት ውስጥ 60 በመቶ የሚሆነው ዉኃ ነው። ደማችንም 90 በመቶ
ዉኃ ነው። ህዋሶቻችን፣ የተለያዩ የሰውነት ክፍሎቻችንና ጡንቻዎቻችን ተግባራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ በቂ ዉኃ
ያስፈልጋቸዋል። የሰውነታችን የሙቀት መጠን እንዲመጣጠን ዉኃ ትልቅ ጠቀሜታ አለው። ምክንያቱም ሰውነታችን በትንፋሽ፣
በሽንትና በላብ በርካታ ዉኃ ያስወጣል። ይህን ዉኃ የምንተካው ፈሳሽነት ያላቸውን ምግቦች በመውሰድና ዉኃ በመጠጣት ነው።

ዉኃ የምግብ አፈጫጨት ሥርዓትን ለመጠበቅ የሚያስችል ንጥረ ነገር ነው። የተመገብናቸው ምግቦች እንዲሰባበሩና ማዕድናትና
ንጥረነገሮች እንዲሟሙ የሚያደርገው ዉኃ ነው። ቆሻሻና አላስፈላጊ ነገሮች ከሰውነታችን ውስጥ እንዲወገዱም ያደርጋል።
ሰውነታችን በላብና በሽንት አማካይነት የቆሻሻ ቅንጣቶች እንዲወገዱ የሚያደርገው በዉኃ አማካይነት ነው።

ëëë እስካሁን ከተገለጹት ሌላ ዉኃ ለምን የሚጠቅም ይመስላችኋል? ëëë

የሰውነታችንን ንጽህና ልንጠብቅ የምንችለው በዉኃ ብቻ ነው። ልብሳችንና ገላችን ሲቆሽሽ በማጽዳት ከተለያዩ በሽታዎችና
መጥፎ ጠረን የምንላቀቀው በዉኃ ነው። ምግብ ለማዘጋጀትም ዉኃ በጣም አስፈላጊ ነው። አብዛኛዎቹ ምግቦቻችን ያለዉኃ
የማይዘጋጁ መሆናቸው የዉኃን ጠቀሜታ ከፍ ያደርገዋል።

አምርተን ልንበላ፣ አጭደን ልንቅም የምንችለው አዝርዕቶቹ በቂ ዉኃ ሲያገኙ ብቻ ነው። አዝርዕቶች ለምልመው፣ አብበው፣
አሽተውና ጎምርተው ፍሬ እንዲሰጡ ዉኃ ይፈልጋሉ። የሚያድጉትና የሚለመልሙት በዉኃ ነው። ያለ ዉኃ ከእጽዋትና ከእንስሳት
ምርት ማግኘት ከቶውንም አይቻልም።

ከእነዚህ ጠቀሜዎች በተጨማሪ ለኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ፣ ለአሳ ምርትና ለመዝናኛነት ትልቅ ጠቀሜታ አለው።

ስለሆነው ዉኃን በአግባቡ ማስተዳደርና መጠቀም አስፈላጊ ነው። በቤታችን ያለውን የቧንቧ ዉኃ፣ በአካባቢያችን የሚገኙ
ምንጮችን፣ ሀይቆችን፣ ወንዞችንና ባህሮችን በአግባቡ በመንከባከብ ልጠቀምባቸው ይገባል።
(ምንጭ፤ ሄልዝ ላይን ዶት ኮም፣ (መጋቢት 19፣1019) ማሻሻያ ሆኖ የተወሰደ።)

ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. የቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹን ተወያይተው ይመልሳሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. የሚከተለውን ምንባብ ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። እንዳስፈላጊነቱ ደግመው ያንብቡላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ
ሲደርሱ ማንበብዎን ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ በጥሞና ያዳምጣሉ፤ የማዳመጥሂደት ጥያቄውን ይመልሳሉ።]

69 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ %9


ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)
(መ. ከምንባቡ ሐሳቦችን እያወጡ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን እንዲሞሉ ያድርጉ። በዋና ሐሳቡ ሥር ደጋፊ ሐሳቦችን እንዲጽፉ
ያድርጉ፤ የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን ለማሟላት የሚቸገሩ ተማሪዎች ካሉ ምንባቡን ደግመው ሊያነቡላቸው ይችላሉ።)
[ተ. ዋናና ዝርዝር ሐሳቦቹን በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ ላይ ይጽፋሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (5 ደቂቃ)


(መ. ዓረፍተነገሮችን በቃላቱ ትክክለኛ ቅርጽ አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጡ።)
[ተ. ሀ. እንዲመጣጠን፤ ለ. መሟሟት፣ ሐ. ጎምርተው መ. የምንላቀቀው]

7.2.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ከማንበባቸው በፊት በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ውይይት ያደርጋሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “ወንዛችን” የሚለውን ታሪክ ድምጽ ሳያሰሙ ሐሳቡን ለመረዳት እንዲያነቡ ያድርጉ፤ ሁሉም ተማሪዎች ማንበባቸውን
ያረጋግጡ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በቃላቸው ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ቃላቱ የተለያየ ፍቺ እንዲሰጡ አድርገው ዓረፍተነገር ያሰሯቸው። የቀረቡት ቃላት ኹለት ትርጉም የሚሰጡ መሆናቸውን ልብ
ይበሉ።)
[ተ. ጠልፎ - የመስኖ ዉኃ ጠልፎ አትክልቶችን ማልማት ይቻላል።
- ሰዎችን ያለፈቃዳቸው ጠልፎ መውሰድ በህግ ያስጠይቃል።]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. በዓረፍተነገሮቹ ለተሰመረባቸው ቃላት ተቃራኒያቸውን መርጠው በቃላቸው እንዲያዛምድ ያድርጉ።)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላት ተቃራኒ ፍቺ በቃላቸው ይሰጣሉ።]

70 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ &


7.2.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ለማስታወስ ያህል ታሪኩን ደግመው ያንብቡላቸው።)
[ተ. ታሪኩን ደግመው በጥሞና ያዳምጣሉ፤ ያለፈውን ያስታውሳሉ።]

ድኅረማዳመጥ (8 ደቂቃ)
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ባዳመጡት ምንባብ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ
ሊሰጧቸው ይችላሉ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ወንዛችን” የሚለውን ታሪክ በተናጠል በትክክልና በፍጥነት እንዲያነቡ ያድርጉ። ሁሉንም ተማሪዎች ለማስነበብ ይሞክሩ።
ከሶስተኛ ክፍል ማስተማሪያ መጻህፍት የአቀላጥፎ ማንበብ መመዘኛ ቼክሊስቶችን በመጠቀም የተማሪዎቹን የማንበብ
ፍጥነትና ትክክለኛነት ይመዝኑ።)
[ተ. “ወንዛችን” የሚለውን ታሪክ በተናጠል በትክክልና በፍጥነት ያነባሉ።]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. የዚህ ተግባር ዓላማ ግሶችን እንዲለዩና እንዲጠቀሙ ማድረግ ነው።፡ ስለሆነም ግሶቹን ተጠቅመው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ
ያድርጉ። ተጨማሪ ምሳሌዎችንና ተግባራትን ይስጡ።)
[ተ. ግሶችን ይለያሉ፤ ግሶቹን ተጠቅመው ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

7.2.4 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን በለሆሳስ እንዲያነቡ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. የተሰጠውን ታሪክ በየግላቸው ለመረዳት ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. ያነበቡትን ታሪክ መሠረት አድርገው ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

71 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ &1


ቃላት (10 ደቂቃ)
(መ. ለተሰጡት ቃላት መዝገበቃላዊ ፍቺ እንዲሰጡ መመሪያ ይስጡ። የመዝገበቃላትን አጠቃቀም በድጋሚ ያሳዩኣቸው።)
[ተ. ለቃላቱ የመዝገበቃላት ፍቺ ይሰጣሉ። መልሳቸውን ለመምህር ያቀርባሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. በዓረፍተነገሮቹ ለተሰመረባቸው ቃላት በታሪኩ መሠረት አውዳዊ ፍቺ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላት አውዳዊ ፍቺ ይጽፋሉ።]

7.2.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

የቃላት አጠቃቀም (20 ደቂቃ)


1ኛ. (መ. በዓረፍተነገሮቹ መጨረሻ ተስማሚ ግስ እንዲጽፉ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጧቸው።)
[ተ. ዓረፍተነገሮቹን በተስማሚ ግሶች ያሟላሉ።]
2ኛ. (መ. የተሰጡትን ግሶች ተጠቅመው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጉ። ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. በተሰጡት ግሶች ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


መ. (ጅምሩን አንቀጽ በተገቢ ሐሳብ አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ጅምሩን አንቀጽ በተገቢ ሐሳብ አሟልተው ይጽፋሉ።]

7.3.1 ማዳመጥ (25 ደቂቃ) የቤት ሥራ

የቤት ሥራ

የአራተኛ ክፍል ተማሪ ነኝ። ባለፈው ሳምንት የአካባቢ ሳይንስ መምህራችን የቤት ስራ ሰጥተውናል። “የዉኃ መገኛዎች ምን ምን
ናቸው?” ይላል የቤት ስራው። እኔ የተወሰነ ሞክሬዋለሁ። ግን ታላላቆቻችሁን ጠይቃችሁ እንድትመጡ ስለተባልን እማዬን ለመጠየቅ
ፈለግሁ።

እማዬ በወረዳችን የዉኃ ጽህፈትቤት ውስጥ ባለሙያ ናት። ስለዉኃ በቂ ግንዛቤ እንዳላት አምናለሁ። ስለሆነም “እማዬ!” አልኳት።
“አቤት” አለችኝ። “አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ” አልኳት። “ምን ዓይነት ጥያቄ ነው?” አለችኝ። “የቤት ስራ የተሰጠሁት ነው” አልኳት።
እርሷም በራስ መተማመን ስሜት “ጠይቀኝ” አለችኝ። ጥያቄውን አነበብኩላት። ቀላል ጥያቄ እንደጠየኳት ገብቶኛል። “ይህንማ ራስህ
አትሰራውም እንዴ?” አለችኝ። እኔም “ሞክሬዋለሁ ግን ሰፋ ያለ ማብራሪያ ለማግኘት ስለፈለግሁ ነው” አልኳት።

“ዉኃ ከምን ከምን ይገኛል አይደል ያልከኝ?” በማለት ጠየቀችኝ። “አዎ!” አልኳት። “ዉኃ በተለያዩ መንገዶች ልናገኝ እንችላለን።
ከምንጭ፣ ከጉድጓድ፣ ከዝናብ፣ ከወንዝ፣ ከባህር፣ ከሃይቅና ከውቅያኖስ እናገኛለን” አለችኝ። እኔም “እሽ እማዬ አመሰግናለሁ! ከዝናብ
ዉኃ እንዴት ልናገኝ እንደምንችል ልታብራሪልኝ ትችያለሽ?” አልኳት። እማዬ ጊዜ ሳታባክን ማብራሪያዋን ቀጠለች። “ዉኃ ከእፅዋትና
ከሌሎች ዉኃማ አካላት በፀሐይ ሙቀት አማካይነት ይተናል። በትነት መልክ የወጣው ዉኃ ሞቃትና ቀላል ስለሆነ ወደከፍተኛ ቦታ

72 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ &2


በመጓዝ ከባቢአየር ውስጥ ይገባል። ከዚያም ወደደመናነት ይለወጣል። በመጨረሻም ዝናብ ሆኖ ይዘንባል። እኛም በዚህ መልኩ
የዝናብ ዉኃ እናገኛለን” አለችኝ። እማዬ ስትናገር ስለማትጣደፍ ሐሳቦቹን አንድ በአንድ በማስታወሻዬ ላይ አሰፈርኩ። በቂ ሐሳብ
ስላገኘሁ ደስ አለኝ። እማዬን አመስግኜ ሐሳቦቹን እያቀናጀሁ ደብተሬ ላይ መመዝገብ ጀመርኩ።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ከተማሪዎችጋር ይወያዩ። ጥያቄዎቹ የተማሪዎቹን የቀደመዕውቀት ለመቀስቀስ የቀረቡ
ስለሆኑ እርስዎ መልስ አይስጡ።)
[ተ. ታሪኩን ከማንበባቸው በፊት በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ከመምህር ጋር ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. የሚከተለውን ምንባብ ረጋ ብለው በጥሩ አገላለጽ ያንብቡላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ጥያቄ ይጠይቋቸው።
ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ። እንዳስፈላጊነቱ ይድገሙላቸው።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ በጥንቃቄ ያዳምጣሉ። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄውን ይመልሳሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ባዳመጡት ምንባብ መሠረት የሐሳብ ማደራጃ ቢጋር አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።
የታሪኩን መጀመሪያ መሀልና መጨረሻ ሁነቶች እንዲጽፉ ያበረታቷቸው።)
[ተ. ባዳመጡት ታሪክ መሠረት የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን ይመልሳሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. በዓረፍተነገሮቹ የተሰመረባቸውን ቃላት በተመሳሳይ ቃላት እንዲተኩ ያድርጉ።)
[ተ. የተሰመረባቸውን ቃላት በተመሳሳይ ቃላት ይተካሉ።]
(መ. ለቀረቡት ቃላት ከምንባቡ ውስጥ አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ ።)
[ተ. በምንባቡ መሠረት ለቃላቱ አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ።]

7.3.2 አንብቦ መረዳት (25 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸውጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ውይይት ያደርጋሉ።]

የማንበብ ሂደት (8 ደቂቃ)


(መ. “ጥቁር እንግዳ” የሚለውን ታሪክ ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው ለመረዳት እንዲያነቡ ያድርጉ፤ ሁሉም ተማሪዎች ስለማንበባቸው
ርግጠኛ ይሁኑ።)
[ተ. ታሪኩን ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው ለመረዳት ያነባሉ።]

73 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ &3


ድኅረንባብ (14 ደቂቃ)
(መ. ቅደምተከተላቸው የተዘበራረቁ ዓረፍተነገሮችን በቅደም ተከተል አስተካክለው እንዲጽፉ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ
ይስጡ።)
[ተ. የተዘበራረቁ ዓረፍተነገሮችን በቅደምተከተል አስተካክለው ይጽፋሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. በተሰጡት ቃላት ላይ -ኦች ወይም -ዎች ቅጥያዎችን በመጨመር ወደ ብዙ ቁጥር እንዲቀይሩ ያድርጉ፤ በሳድስ በሚጨርሱት
ቃላት ላይ /-ኦች/፣ በአናባቢ በሚጨርሱ ቃላት ላይ ደግሞ /-ዎች/ እንደሚጨመር ልብ ይበሉ።)
[ተ. በቃላት ላይ -ኦች ወይም -ዎች በመጨመር ወደብዙ ቁጥር ይቀይራሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. በቀረቡት ቃላትና ሐረጋት ዓረፍተነገር በመስራት አውዳዊ ፍቻቸውን እንዲያሳዩ ያደርጉ።)
[ተ. ባልና ሚስቱ ከዚህ በፊት ውኃ ከጉድጓድ እንደሚወጣ ሰምተው ስለማያውቁ ግርአላቸው።
ፍቺው “ግራ ገባቸው” ማለት ሲሆን ይህን ፍቺ ያስገኙት አውድ ከዚህ በፊት እና ስለማያውቁ የሚሉት ናቸው።
[ተ. ሰዎቹ ለአካባቢው እንግዳ ስለሆኑ መንገዱ ግርአላቸው ። “ጠፋቸው” የሚል ፍቺ ያለው ሲሆን ፍቺውን ያስገኘው ለአካባቢው
እንግዳ መሆን የሚለው ሐረግ ነው።)

7.3.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (8 ደቂቃ)


(መ. የማዳመጥ ታሪኩን ደግመው ያንብቡላቸው።ተማሪዎቹ እንዲያዳምጡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በአስተውሎት ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (7 ደቂቃ)
(መ. የዝናብ ውኃ አፈጣጠር ዑደትን የሚያሳይ የቢጋር ሠንጠረዥ በደብተራቸው ሠርተው እንዲያሟሉ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ጥቁር እንግዳ” የሚለውን ታሪክ ሞዴል ሆነው ያንብቡላቸውና በተናጠል ድምፅ እያሰሙ አቀላጥፈው እንዲያነቡ
ያለማምዷቸው።)
[ተ. ሞዴል ንባቡን መነሻ በማድረግ ታሪኩን አቀላጥፈው ማንበብን ይለማመዳሉ።]

74 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ &4


መጻፍ (15 ደቂቃ)
(መ. መነሻ ሐሳቡን መሠረት በማድረግ አንድ የተሟላ አንቀጽ እንዲጽፉ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. ቤታችን ረባዳማ ቦታ ላይ ነው። ከቤታችን በላይ ካለው ኮረብታ ሥር የምትፈልቅ ትንሽ ምንጭ አለች። ምንጯ በበጋም
አትደርቅም። ታዲያ አባቴ ከብቶች እየገቡ ያበላሿታል እያለ በእንጨት አጥሯታል። ከምንጯ ዉኃ በጀሪካን እየቀዳን የተለያዩ
አትክልቶችን በጓሯችን አልምተናል። ለምሳሌ፡-ጎመን፣ቲማቲም፣ካሮትና ድንች ይቀጠሳሉ። የዘራነው የበቆሎ እሸትም እስከ
ጎረቤቶቻችን በቅቶናል። ለልብስ ማጠቢያም ሆነ ለመጠጥ ከበጋ እስከክረምት አናስብም። ከብቶቻችንንም ዉኃየምናጠጣው
ከዚችው ምንጭ እየቀዳን ነው። በአጠቃላይ የእኛ ህይወት በዚች ምንጭ ላይ የተመሰረተ ነው ማለት ይቻላል።]

7.3.4 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች ታሪኩን ድምጽ ሳያሰሙ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን “ጥቁር እንግዳ” በሚለው ታሪክ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ
ይስጡ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


1ኛ. (መ. በተሰጡት ቃላት ላይ ያሉትን ብዙ ቁጥር አመልካች ቅጥያዎች ለይተው እንዲያወጡ ያድርጉ፤ ምሳሌ ሠርተው
ያሳዩአቸው። መልሶቹ እንደሚከተለው ተሰጥተዋል።)
[ተ. ሀ. -ዎች. ሐ. -ኦች ሠ. - ኦች
ለ. -ኦች መ. -ኦች ረ. -ዎች]
2ኛ. (መ. በቃላት ላይ “-ኦች” እና “-ዎች” ን በመጨመር ወደብዙ ቁጥር እንዲለውጡ ያድርጉ።)
[ተ. በቃላቱ ላይ “-ኦች” እና “-ዎች” ን በመጨመር ወደብዙ ቁጥር ይለውጣሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. በቀረቡት ቃላት ዓረፍተነገር በመስራት አውዳዊ ፍቻቸውን እንዲያሳዩ ያድርጉ።)
[ተ. በታሪኩ ውስጥ ባላቸው አውዳዊ ፍቺ መሠረት በቃላቱ ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ። ]

75 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ &5


7.3.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (15 ደቂቃ)


(መ. በቀረበው ርዕሰጉዳይ በጥንድ እንዲወያዩ ያድርጉ። በውይይት ወቅት ተራን ጠብቆ መናገር እንደሚገባ ያስታውሷቸው።)
[ተ. በቀረበው ርዕሰጉዳይ ላይ ርስበርስ ይወያያሉ።]

መጻፍ (5 ደቂቃ)
(መ. ሥርዓተነጥቦች ተጠቅመው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጉ። ምሳሌዎችን በመስጠት የቀረበውን የሥርዓተነጥብ ማስታወሻ
ያብራሩላቸው።)
[ተ. ሥርዓተነጥቦችን በዓረፍተነገሮቹ ውስጥ በተገቢ ቦታ በማስገባት ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

76 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 7 ዉኃ &7


ምዕራፍ ድርድር
8

የምዕራፉ ዓላማዎች

ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-


ƒƒ ሌሎችን እያዳመጡና ለሌሎች ተራ እየሰጡ ይናገራሉ፤
ƒƒ ምንባቡን በግል በማንበብ ዝርዝር ጉዳዮችን ያብራራሉ፤
ƒƒ የትምህርትቤታቸውን ህግና ደንብ ይፅፋሉ፤
ƒƒ የመነሻ ቅጥያዎችን ከቃላት ላይ ይነጥላሉ።

8.1.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) የአባጋር የእርቅ ሥርዓት

የአባጋር የእርቅ ሥርዓት

በብዙዎች ዘንድ ፊት ተነስቶት የነበረና በሂደት ግን ፍቱን አዋጭነቱ እየታመነበት የመጣ ነው- ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓት።
እንዲጐለብቱ ከሚፈለጉት ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶቻችን አንዱ የአባጋር የእርቅ ሥርዓት ነው። “እምባ የሚደርቀዉ በፍርድ
ሳይሆን በፍቅር ነው” ይላሉ የአባጋር ሥርዓት ተከታይ አባቶች። አባጋር በአንባሰል ወረዳ የሚዘወተር ቢሆንም በሌሎች የደቡብና
የሰሜን ወሎ አካባቢዎችም ተግባራዊ የሚደረግ የግጭት አፈታት ሥርዓት ነው።

አባጋር ማለት በአካባቢው አጠራር የተጣላ የሚታረቅበትና አጥፊው በሀገር ሽማግሌዎች ፊት “ተው” የሚባልበት ሥርዓት ነው።
ዱአ አድርገው ከተጣሉት ሰዎች መካከል ጥልን የሚያባርሩበት ሰርዓት ነው። አባጋር የሚለው ቃል በቃል ሲተረጐም ደግሞ የሀገር
ራስ፣ መሪ፣ አስታራቂ የሚል ፍቺ አለው።

የአባጋር የእርቅ ሥርዓት ከሃይማኖትና በባህል ጋር የተሳሰረ ነው። በአካባቢው የሚኖሩ ሰዎች በተለያዩ አለመግባባቶች ቅራኔ ውስጥ
ይገባሉ። ወይም ነብስ ሊያጠፉ ይችላሉ። በዚህ ወቅት የአካባቢው ሽማግሌዎችና ኗሪዎች እርቅ እንዲመጣ ከሳምንት እስከ አንድ ወር
ድረስ ፈጣሪያቸውን እየተለማመኑ የሚያካሂዱት ሥርዓት ነዉ። የአባጋር ሥርዓት ሲከናወን አንድ ገዳይ ሰው ገድሎ ከጠፋ የገዳይ
ቤተሰቦች ከሟች ቤተሰቦች ጋር አስታርቁን ብለው በአባጋር ቦታ ይቀመጣሉ። እርቁ ካልተፈፀመ በስተቀር የገዳዩ ቤተሰቦች ከዚያ
ቦታ አይነሱም።

ëëë ጥፋተኛ የሆነው ሰው ከአካባቢው ቢሰወር ምን የሚደረግ ይመስላችኋል? ëëë

77 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር &7


ገዳዩ ነብስ አጥፍቶ ከአካባቢው ቢሰወር እንኳን ከሌሎች አካባቢ አባጋር ጋር በመነጋገር ካለበት ቦታ ተይዞ እንዲመጣ ተደርጐ
እርቁ ይካሄዳል። በሌላ አካባቢ ነብስ አጥፍቶ መምጣቱ የሚታወቅ ሰው ካለ በአካባቢዉ ወደሚገኝ አባጋር ሄዶ እርቅ እንዲያወርድ
ይልኩታል፤ ይገፋፉታል እንጅ ደብቀዉ አያስቀምጡትም። አባጋር ለእርቅ ከተቀመጡ ገዳይ መጥቶ እርቁ እስካልተፈፀመ ድረስ ከዚያ
ቦታ አይነሱም። ፈጣሪያቸውን እየተለማመኑ አጥፊዉ እስኪመጣ ይጠብቃሉ።

በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ ይስማ ንጉሥ አካባቢ የሚገኙ አባጋሮች የእርቅ ሥርዓት በእስልምና እምነት ተከታዮች የሚካሄድ
ነው። በደሴ ዙሪያ አንዳንድ አካባቢዎችም በክርስትና እምነት ተከታዮች የሚከናወን የአባጋር ሥርዓት ይገኛል።

የአባጋር ሥርአት ሲከናወን ገዳይ ወይም የተገደለበት ቤተሰብ የተለያዩ እምነት ተከታይ ቢሆኑም ሁሉም በአባጋር ሥርአት ይገዛሉ።
ምክንያቱም ሁሉም የሀገር ወግና ደንብ ባህል ስለሆነ በአባጋር አማካኝነት እርቁ ይካሄዳል። የክርስትና እምነት ተከታይ ቢሆንም
መስቀል ይዘዉ አብረውት ካህናት በተገኙበት እርቁ እንዲካሄድ ይደረጋል። ይህም ሁለቱም እምነቶች በመከባበርና በመቻቻል
አብረው መኖራቸውን ያሳያል።
(ቱር ኢን ኢትዮጵያ። ሚያዘያ 1 2019። ከሚል ድረገጽ ከፊል ማሻሻያ ተደርጎበት የተወሰደ)

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመ ማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከተማሪዎች ጋር ይወያዩ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ያደርጋሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ምንባቡን ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። እንዳስፈላጊነቱ ሊደግሙላቸው ይችላሉ። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ
ማንበብዎን ለአፍታ ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. ታሪኩን በአስተውሎት ያዳምጣሉ። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄውን ይመልሳሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ጥያቄዎቹን “እውነት” ወይም “ሀሰት” ብለው እንዲመልሱ ያድርጉ። ለመልሳቸው ምክንያት እንዲሰጡ ይጠይቋቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን እውነት ወይም ሀሰት በማለት በምክንያት ይመልሳሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (20 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላት የተለያየ ፍቺ ዓረፍተነገር እንዲሰሩ ያድርጉ። ምሳሌውን ያሳዩአቸው።)
[ተ. በቃላቱ የተለያየ ፍቺ ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]
(መ. በ “ሀ” ክፍል ለቀረቡት ቃላት ተመሳሳያቸውን ከ “ለ” ክፍል መርጠው እንዲያዛምዱ ያድርጉ፤ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

78 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር &8


8.1.2 አንብቦ መረዳት (25 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ። )
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን በለሆሳስ እንዲያነቡ ያድርጉ። ሁሉም ተማሪዎች ማንበባቸውን ይከታተሉ)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው በለሆሳስ ለመረዳት ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. የተሰጡትን ሐረጋት በታሪኩ መሠረት አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር እንዲሰሩ ያድርጉ።
[ተ. በአባጋር ሽምግልና የተጎጂ ቤተሰቦችን እንባ ማድረቅ ይቻላል። “ማጽናናት፣ መካስ” የሚል ፍቺ ያለው ሲሆን ይህን ፍቺ
ያስገኘው የተጎጂ ቤተሰቦች የሚለው ነው።]

የቃላት አጠቃቀም (8 ደቂቃ)


(መ. ዓረፍተነገሮቹን ተስማሚ ቃላት ከሳጥኑ ውስጥ በመምረጥ እንዲያሟሉ ያድርጉ።)
[ተ. ዓረፍተነገሮቹን ተስማሚ ቃላትን በመምረጥ አሟልተው ይጽፋሉ።]

8.1.3 ማዳመጥ (10 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (3 ደቂቃ)


(መ. ምንባቡን ያንብቡላቸው።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡላቸው በአስተውሎት ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (7 ደቂቃ)
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹ በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

79 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር &9


አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
(መ. “እርቅ ማውረድ” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ መመሪያ ይስጡ።
ሁሉም ተማሪዎች ማንበባቸውን ይከታተሉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. በሐሳብ ማደራጃ ቢጋር ውስጥ ያሉትን ነጥቦች መነሻ አድርገው የተሟላ አንቀጽ እንዲጽፉ መመሪያ ይስጡ። በእያንዳንዱ
የመፃፍ ሂደት ደረጃዎች ላይ እየተዘዋወሩ ተማሪዎችን ይደግፉ፤ ተገቢ ግብረመልስም ይስጡ።)
[ተ. የተሰጡትን ነጥቦች መነሻ በማድረግ የተሟላ አንቀጽ ይጽፋሉ።]

8.1.4 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው እንዲያነቡ ያድርጉ። ሁሉም ተማሪዎች ስለማንበባቸው ርግጠኛ ይሁኑ።)
[ተ. ታሪኩን እየተገነዘቡ በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን ትክክለኛ መልስ በመምረጥ እንዲመልሱ ያድርጉ። ለመልሳቸው ማብራሪያ ይጠይቁ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በመምረጥ ይመልሳሉ።]

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. በ “ሀ” ክፍል የቀረቡትን ቃላት ተቃራኒያቸውን ከ “ለ” ክፍል እየመረጡ እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን ከተቃራኒያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]
(መ. ዋና ቃሉንና ቅጥያዎቹን ለይተው እንዲያወጡ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)

[ተ.] መልስ፡- ሀ. [መ. አለ- መቻል -ኣቸው] መ. [መ. ተ- ቸረ -ኣቸው]


ለ. [መ. አውድ -ኣዊ] ሠ. [መ. ጎረቤት-ኣም-ኦች-]
ሐ. [መ. ሽማግሌ -ዎች-ኡ] ረ. [መ. ነገር- ኡ-ኣቸው]

80 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር W


የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)

ማስታወሻ
ተማሪዎችን በቡድን አደራጅተው ለሚቀጥለው ቀን እንደሽማግሌና እንደታራቂዎች ሆነው አጭር ድራማ አዘጋጅተው እንዲመጡ
የቤት ሥራ ይስጧቸው።

(መ. ዓረፍተነገሮቹን በቅንፍ ውስጥ ካሉት ቃላት ትክክለኛውን እየመረጡ እንዲያሟሉ ያድርጉ።
[መልስ ሀ. [ተ. ጠርቶ] ለ. [ተ. አሳውቆ] ሐ. [ተ. ወድቀው] መ. [ተ. እያስታወሱ]

8.1.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (25 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎችን በቡድን አደራጅተው እንደሽማግሌና እንደታራቂዎች ሆነው አጭር ድራማ እንዲሰሩ ያድርጉ፤ስራውን ቀድመው
የቤት ስራ ሊሰጡ ይገባል።)
[ተ. እንደሽማግሌና እንደታራቂዎች ሆነው ድራማ በመስራት ሚና ጨዋታን ይጫወታሉ።]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. “እርቅ ማውረድ” የሚለውን ታሪክ ሐሳብ በማጠቃለል በአንድ አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉ። ስለማጠቃለያ አጻጻፍ
ያስታውሷቸው።)
ለምሳሌ፡- [ተ.ታሪኩን ደጋግሞ ማንበብ፤ ዋናውን ሐሳብ ማውጣት፤ ደጋፊ ነጥቦችን መለየ ወዘተ.]

ሰማይ ቢቀደድ ሽማግሌ


8.2.1 ማዳመጥ (25 ደቂቃ)
ይሰፋዋል
ሰማይ ቢቀደድ ሽማግሌ ይሰፋዋል

ሽምግልና ኹለትና ከዚያ በላይ በሆኑ ሰዎች አማካይነት የሚከናወን ጥላቻን አርቆ ፍቅርንና ይቅርታን በልብ ውስጥ ለመዝራት
የሚፈጸም ባህላዊ የእርቅ ሥርዓት ነው። ኢትዮጵያውያን ለሽምግልና ትልቅ ክብር ይሰጣሉ። በሽምግልና ያምናሉ፤ ችግሮቻቸውን
በሽምግልና ይፈታሉ። ቂምና ቁርሾ ሁሉ የሚሽረው በሽምግልና ስለመሆኑ ጽኑ እምነት አላቸው።

በአገራችን ሽምግልና ካለው ክብርና ተቀባይነት አንጻር “ሰማይ ቢቀደድ ሽማግሌ ይሰፋዋል” ይባላል። በባህላችን ከሽምግልና
የሚያመልጥ ነገር እንደሌለ ይታመናል። እንዲያውም ሽምግልና አመጣጡ ከሰው ልጅ አብሮነት ጋር እንደሆነም ይገለጻል። ሰው
ከሰው ጋር አብሮ ሲኖር ግጭት ይፈጠራል። እናም ያ ግጭት እየከረረ ሄዶ ቂምና ቁርሾ እንዳይያዝበትና አደጋ እንዳያስከትል
የሽምግልና ሚና ላቅ ያለ ነው። ሽምግልና የሰው ነፍስ እንዳይጠፋ፣ ሰላም እንዲሰፍንና አንድነት እንዲጠናከር ያደርጋል። በሽምግልና
ሥርዓት የተፈጸሙ ወንጀሎች ይጣራሉ፣ አጥፊውና የበደሉ መጠን ይለያል። በዳይና ተበዳይ ከተለዩ በኋላ ለበደሉ ካሳ ይጣላል።
በመጨረሻም “አንተም ተው፣ አንተም ተው” በሚል የተጣሉ እንዲታረቁ ይደረጋል። በዚህ መልኩ ደም የተቃቡ ሰዎችም ሳይቀሩ
እርቅ እንዲያወርዱ ሽምግልና ወሳኝ ሚና ይጫወታል።

81 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር W1


ëëë በሽምግልና የሚመረጡ ሰዎች ምን አይነት ናቸው ëëë

ሽምግልና በግጭት ምክንያት የተጣላን ሁሉ የማስማማት ጉዳይ ነው። ስለሆነም እንዲያሸማግሉ የሚመረጡ ሰዎች በእድሜ ከፍ ያሉ
ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች መስፈርቶችንም የሚያሟሉ ሊሆኑ ይገባል። በማህበረሰቡ ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው፣ የሚፈሩ፣ የሚደመጡና
የሚታፈሩ ሊሆኑ ይገባል። ተናግረው የሚያሳምኑ፣ አንደበተርቱዕና ነገር አዋቂ መሆንም ይጠበቅባቸዋል። የመምከርና የመመረቅ ፀጋ
የተሰጣቸው እንዲሆኑም ይፈለጋል። ሽማግሌዎቹ እነዚህ ችሎታዎች ያሏቸው ከሆኑ ተሸማጋዮቹ ጊዜ ሳይወስዱ እርቁን ይቀበሉታል፤
ይቅርታቸውም ከልብ ይሆናል።
(ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ሰኔ 14/2012 ማሻሻያ ተደርጎ የተወሰደ)

ቅድመማዳመጥ (4 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ። አይነስውራን ተማሪዎች ካሉ ስለስዕሉ ጓደኞቻቸው
እንዲገልፁላቸው ያድርጉ ወይም ርስዎ ይግለፁላቸው። ከዚያም ግምታቸውን ሊጠይቋቸው ይችላሉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ርስበርሳቸው ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (8 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎችን ለማዳመጥ ዝግጁ ያድርጉ። ታሪኩን ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። እንዳስፈላጊነቱ ይድገሙላቸው። የማዳመጥ
ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ማንበብዎን ለአፍታ ያህል ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ወዲያው ንባብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ በአስተውሎት ያዳምጣሉ። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄውን ይመልሳሉ]

ድኅረማዳመጥ (13 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን ባዳመጡት ምንባብ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. ለተሰመረባቸው ቃላት ተመሳሳይ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላት ተመሳሳይ ፍቺ ይሰጣሉ።]
(መ. በ “ሀ” ክፍል የቀረቡትን ብያኔዎች በ “ለ” ክፍል ካሉት ቃላት ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. የተሰጡትን ቃላት በማዛመድ ይመልሳሉ።]

8.2.2 አንብቦ መረዳት (25 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ይወያያሉ።]

82 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር W2


የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
(መ. “ትዝታዬ” የሚለውን ታሪክ በለሆሳስ እንዲያነቡ መመሪያ ይስጡ፤ ሁሉም ተማሪዎች ማንበባቸውን ይከታተሉ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (12 ደቂቃ)


(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድህረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]
(መ. የተዘበራረቁ ዓረፍተነገሮችን በቅደምተከተል አስተካክለው እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የተዘበራረቁትን ዓረፍተነገሮች አስተካክለው በቅደምተከተል ይጽፋሉ።]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. በምሳሌው መሠረት የቃላቱን ዋናቃልና ቅጥያዎች ነጣጥለው እንዲያወጡ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ቅጥያዎቹን ከዋናው ቃል ላይ ለያይተው ይጽፋሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (8 ደቂቃ)


(መ. በ “ሀ” ክፍል ለቀረቡት ቃላት ተመሳሳያቸውን ከ “ለ” ክፍል መርጠው እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላትን ከተመሳሳያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

8.2.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. የማዳመጥ ምንባቡን ደግመው ያንብቡላቸው።)
[ተ. ታሪኩ ተደግሞ ሲነበብ በጥሞና ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (8 ደቂቃ)
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ባዳመጡት ምንባብ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ)።
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ትዝታዬ” የሚለውን ታሪክ ጥንድ ሆነው በመጋራት አቀላጥፈው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ በመጋራት አቀላጥፈው ያነባሉ። ርስበርሳቸው ይተጋገዛሉ።]

83 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር W3


መጻፍ (15 ደቂቃ)
(መ. በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ ውስጥ የተሰጡትን ነጥቦች መነሻ በማድረግ ሦስት አንቀጽ ያለው ድርሰት እንዲጽፉ ያድርጉ።
በቅድሚያ ሐሳባቸውን ባጭርባጭሩ እንዲዘረዝሩ ያድርጉ። ከዚያም ሐሳባቸውን በቅደምተከተል እንዲያደራጁና እያስፋፉ
እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. በተሰጡት ነጥቦች መሠረት ሦስት አንቀጽ ያለው ታሪክ ይጽፋሉ።]

8.2.4 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ለመረዳት በየግላቸው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን ባነበቡት ታሪክ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ መመሪያ ይስጡ።)
መልስ፡- ሀ. [ተ. ቆላ አካባቢ ይመስለኛል፤ ምክንያቱም ታሪኩ ፍየል ብቻ ያለበትና በግ የሌለበት ስለሚል።]
ለ. [ተ. ቀደም ባሉት ዘመናት ነው፤ ምናልባትም በ1990ዎቹ ሳይሆን አይቀርም)

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. ቃላት በታሪኩ ውስጥና ከታሪኩ ውጪ ያላቸውን ፍቺ የሚያሳዩ ዓረፍተነገሮችን እንዲመሠርቱ ያድርጉ። ምሳሌውን ማየት
ይቻላል።)
[ተ. ቃላቱ ከታሪኩ ውጪ ባላቸው ፍቺ ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. አብረው የሚሄዱ ቃላትን በመምረጥ እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. አንድላይ የሚሄዱ ቃላትን በመምረጥ ያዛምዳሉ።]

8.2.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (15 ደቂቃ)


(መ. በተሰጠው ርዕሰጉዳይ ላይ በቡድን እንዲወያዩ መመሪያ ይስጡ። የዚህ ክፍለጊዜ አላማ ንግግርን ማዳበር ነው።)
[ተ. በተሰጠው ርዕሰጉዳይ ላይ በቡድን ይወያያሉ።]

84 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር W4


መጻፍ (25 ደቂቃ)
(መ. “የክረምት ትዝታዬ” በሚል ርዕስ ተማሪዎች ስለክረምት ትዝታቸው ባለሦስት አንቀጽ ድርሰት እንዲፅፉ ያድርጉ።ሐሳብ
ከማፍለቅ ጀምሮ ረቂቅ እንዴት እንደሚያዘጋጁና እንደሚከልሱ ለተማሪዎች ተገቢ ማብራሪያ ይስጡ። በሂደቱም ተገቢ ድጋፍ
ያድርጉ፤ ግብረመልስም ይስጡ።)
[ተ. “የክረምት ትዝታዬ” በሚል ርዕስ አጭር ድርሰት ይጽፋሉ። የጻፉትንም ለመምህራቸው ያሳያሉ።)

8.3.1 ማዳመጥ (25 ደቂቃ) ገንዘብ ለህፃናት

ገንዘብ ለህፃናት
ቡሬ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ባልና ሚስት ነበሩ። ለረጅም ዓመታት በፍቅርና በመተሳሰብ ይኖሩ ነበር። አራት ልጆችን አፍርተዋል።
ሁለቱ ወንዶች ናቸው። የመጀመሪያ ልጃቸው ገና ስምንት ዓመቱ ነው። በልጆች አስተዳደግ ላይ የተለያዩ አቋሞች በመያዛቸው
ሳቢያ በባልና በሚስት መካከል አልፎ አልፎ አለመግባባቶች ይፈጠሩ ነበር።

ከእለታት አንድ ቀን ለልጆች ብር መስጠት ችግር አለው ችግር የለውም በሚል ክርክር ይጀምራሉ። ሚስት ለልጆች የሚያፈልጋቸውን
ነገር በቤት ውስጥ አዘጋጅተው ወይም ራሳቸው ወላጆች ገዝተው መስጠት እንዳለባቸው እንጅ ብር ሊሰጧቸው እንደማይገባ
ትገልፃለች። ባል ደግሞ ልጆቻቸው ቤት ውስጥ የማያገኙትን ነገር ገዝተው እንዲበሉ ብር ቢሰጣቸው ችግር እንደማይኖርና
ልጆቻቸውም እንደሚደሰቱ ይገልፅላታል። በዚህ ጉዳይ ላይ ያላቸውን አቋም በመወያየት መፍታት እንዳለባቸው ተገነዘቡ።

ታዲያ ሁለቱም ሌላ ጊዜ እንደሚያደርጉት ሁሉ አሳማኝ የሚሏቸውን ሐሳቦች እያቀረቡ መወያየት ጀመሩ። “ልጆቻችን ለጋ
ናቸው። ስለሆነም ለከረሚላ፣ ለዳቦ፣ ለብስኩት፣ ለሙዝ፣ ለብርቱካን ወዘተ እያልን ብር ልንሰጣቸው አይገባም” ስትል ሚስት
ሀሳቧን ገለፀች። ባልም የሚስቱ ሐሳብ የተዋጠለት አይመስልም። ጉሮሮውን እህህም ብሎ ካፀዳ በኋላ “ምን ችግር አለው? ገዝተው
እንዲበሉ ማድረግ ጉዳቱ ምኑ ላይ ነው? ልጆቻችንን እያስደሰትን ማሳደግ አይጠበቅብንም ትያለሽ?” ሲል መልሶ ጠየቃት።

እናትም ማብራሪያ ለመስጠት የሚያስችላትን እድል ስላገኘች ንግግሯን በደስታ ቀጠለች። “የልጆችን ፍላጎት ማሟላትና እንዲደሰቱ
ማድረግ እንደሚገባ አምናለሁ። ልጆቻችን ክፉና ደጉን አልለዩም። ስለሆነም ከፍ እስኪሉ ድረስ የሚያስፈልጋቸውን ራሳችን
እየገዛን ልንሰጣቸው ይገባል። ብር ከለመዱ የተቀመጠ ገንዘብ ማንሳት ይጀምራሉ። ልጆችን ሥርዓት ማስያዝ የምንችለው
ደግሞ እኛው ራሳችን ነን። ለመግዛት ወደሱቅ ሲሄዱስ ቢሆን በመኪና ቢገጩብን ወይም በሌቦች ታፍነው ቢሰረቁብን ማነው
የሚጎዳው?” ስትል ንግግሯን በጥያቄ ቋጨችው። አባት በዚህ መንገድ አስቦት ስለማያውቅ በሚስቱ ብልህነትና አስተዋይነት
በጣም እየተገረመ በሀሳቧ ተስማማ። ለልጆቹ የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ ራሱ እየገዛ ያመጣላቸው ጀመር።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ከማዳመጣቸው በፊት በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎችን ለማዳመጥ ዝግጁ ያድርጉ። ታሪኩን ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። እንዳስፈላጊነቱ ይድገሙላቸው። የማዳመጥ
ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ማንበብዎን ለአፍታ ያህል ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ወዲያው ንባብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንቃቄ ያዳምጣሉ። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄውን ይመልሳሉ።]

85 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር W5


ድኅረማዳመጥ (12 ደቂቃ)
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ባዳመጡት ታሪክ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ይጠይቁ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ
ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. ለተሰመረባቸው ቃላትና ሐረጋት ተመሳሳያቸውን እየመረጡ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. መልስ፡- 1. ለ 2ሀ 3 መ 4መ]
(መ. በተሰጡት ቃላት አውዳዊ ፍች እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር እንዲሠሩ ያድርጉ።)
[ተ. በቃላቱ አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

8.3.2 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ያደርጋሉ።]

የማንበብ ሂደት (8 ደቂቃ)


(መ. “የተከበሩት አባት” የሚለውን ታሪክ በለሆሳስ በየግላቸው እንዲያነቡ ያድርጉ። ሁሉም ተማሪዎች ስለማንበባቸው ርግጠኛ
ይሁኑ።)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው በለሆሳስ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን “እውነት” ወይም “ሀሰት” ብለው እንዲመልሱ ይጠይቁ፤ መልሳቸውን በምክንያት እንዲያስረዱ
ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን እውነት ወይም ሀሰት በማለት በምክንያት ይመልሳሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. በምሳሌው መሠረት ዋና ቃሉንና ቅጥያውን በማጣመር አዲስ ቃል እንዲመሠርቱ ያድርጉ።)
[ተ. ዋና ቃሉንና ቅጥያውን በማጣመር አዲስ ቃል ይመሠርታሉ።]

86 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር W6


የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)
(መ. በዓረፍተነገቹ የተጓደሉትን ቃላትና ሐረጋት ከታሪኩ በመፈለግ አሟልተው እንዲጽፍ ይጠይቁ።)
[ተ. ዓረፍተነገሮቹን አሟልተው ይጽፋሉ።]
መልስ ሀ. [ተ. ስኬቶች] ሐ. [ተ. ከወቀሱ] ሠ. [ተ. ልብ]
ለ.[ተ. ወደከፋ] መ. [ተ. የከረረ ጥል]

8.3.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ)


(መ. በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ያለውን የማዳመጥ ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው።)
[ተ. ታሪኩን በድጋሚ ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. ባዳመጡት ታሪክ መሠረት የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን ያሟላሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (15 ደቂቃ)


(መ. “የተከበሩት አባት” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ። አርዓያ
ሆነው አንድ አንቀጽ ሊያነቡላቸው ይችላሉ።
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

መጻፍ (10 ደቂቃ)


መ. (“የተከበሩት አባት” የሚለውን ታሪክ በአንድ አንቀጽ አሳጥረው እንዲጽፉ መመሪያ ይስጡ፤ ማጠቃለያ እንዴት እንደሚጻፍ
ማስታወሻ ይስጧቸው። በተሰጠው ሰዓት ያልጨረሱ ተማሪዎች ካሉ በቤታቸው አጠናቀው እንዲመጡ ያድርጉ።)
[ተ. የታሪኩን ዋና ሐሳብ በአንድ አንቀጽ አሳጥረው ይጽፋሉ።]

8.3.4 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “የተከበሩት አባት” የሚለውን ታሪክ ደግሞ እንዲያነቡ ያድርጉ)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት በየግላቸው በለሆሳስ ያነባሉ።]

87 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር W7


ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን ባነበቡት ታሪክ መሠረት አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ እገዛ ያድርጉላቸው።)
[ተ. በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ ውስጥ የታሪኩን ሐሳብ ይጽፋሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. በ “ሀ” ክፍል ላሉት ቃላት ከ “ለ” ክፍል ተቃራኒያቸውን መርጠው እንዲያዛምዱ ማድረግ።)
[ተ. ቃላትን ከተቃራኒያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. በዓረፍተነገሮች ለተሰረመባቸው ቃላትና ሐረጋት አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ። ምሳሌ ሠርተው ያሳዩ።) ምሳሌ
[ተ. ሀ. ቆመውበት፡- በሽምግልና ይዘውት]
[ተ. ለ. ኮትኩተው ፡- መክረውና ገስጸው]

8.3.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (15 ደቂቃ)


(መ. የእርቅ ሥርዓት ሰላም ለማስፈን ያለውን አዎንታዊ አስተዋጾ በተመከለተ በቡድን ተወያይተው እንዲያቀርቡ ያድርጉ።)
[ተ. በተሰጠው ርዕስ ላይ ውይይት ያካሂዳሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. ጅምር አንቀጹን አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ፤ የሚከተለውን ምሳሌ ይመልከቱ።)

የአካባቢያችን የእርቅ ሂደት


[ተ. ሰዎች በልዩ ልዩ አጋጣሚዎች ቅራኔ ፈጥረው ጥል ውስጥ ይገባሉ። የእኛ አካባቢ ነዋሪዎችም በተለያየ ጊዜ ተጣልተው
ተቀያይመዋል። ለምሳሌ በመሬት፣ በመንገድ፣ በሳር፣ በመስኖ ውኃ ወዘተ. ምክንያት ግጭት ውስጥ ገብተው ነበር።
ይሁን እንጂ ተጣልተው አልቀሩም። በአስተሳሰብ በሰል ያሉ ትልልቅ ሰዎች ተመርጠው ቀን ይቆረጥና ቀጠሮ ይያዛል። በቀጠሮ
ዕለት የተጣሉት ሰዎች እንዲቀርቡ ይደረጋል። አንዱ ባንድ ወገን ሌላው በሌላ ወገን እየተጋለሉ በደላቸውን ለሽማግሌዎቹ
ይናገራሉ። ሽማግሌዎቹ የሁለቱን ወገኖች ሐሳብ ተራበተራ ከተቀበሉ በኋላ ሁለቱንም አንድ ላይ ጠርተው ያወቃቅሳሉ፤
ያስማማሉ። ካሳ የሚስፈልገው ካለም ያስክሳሉ። ካሳው በርከት ያለ ሆኖ የሚክሰውን ሰው ይጎዳል ብለው ካሰቡም የተወሰነውን
ሽማግሌዎች ይችላሉ ይባላል። ይህም የሚካሰው ሰው የተወሰነውን እንዲተው ለማድረግ ተብሎ የሚደረግ ዘዴ ነው።
በመጨረሻም ወደሁለቱም ቤት ሄደው እህል ውኃ ይቀምሳሉ። በዚህ ሁኔታ የብዙ ሰው ፍቅር ወደነበረበት ተመልሷል።]

88 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 8 ድርድር W8


ምዕራፍ ብዙኃን መገናኛ
9

የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
ƒƒ የተቀረፁ ንግግሮችን አዳምጠው ዋናውን ሐሳብ ይናገራሉ፤
ƒƒ አንድ ጽሑፍ አንብበው የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎችን ይሠራሉ፤
ƒƒ ነጠላ ዓረፍተነገሮችን በመጠቀም አንቀፅ ይፅፋሉ፤
ƒƒ ቃላትን በገቡበት አውድ ይበይናሉ፤
ƒƒ መስተዋድዶችን ተጠቅመው ዓረፍተነገሮችን ይመሠርታሉ።

9.1.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) የመጀመሪያው ጋዜጣ

የመጀመሪያው ጋዜጣ

አዕምሮ በአማርኛ ቋንቋ ይታተም የነበረ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጋዜጣ ነው። አዕምሮ የተመሰረተው በግሪካዊው አንድርያ ካቫዲያ
እ.አ.አ በ1902 ዓ.ም. ነበር። እ.አ.አ. ከ1906-07 ዓ.ም. ይታተም የነበረው ጋዜጣ ባለሦስት ገጽ ዜናንና ባለአንድ ገጽ ማስታወቂያን
ያካተተ ነበር። ዜናው በአውሮፓ ስላለ ጦርነት፣ ስለመሪዎች ጉብኝት እንዲሁም በኢኮኖሚና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ስለተደረጉ
ስምምነቶች የሚያትት ነበር። በሀገር ውስጥ የንጉሱ የስራ እንቅስቃሴ፣ ንግግሮች፣ አዋጆች፣ በከተማው ውስጥ የተከሰቱ አዳዲስ
ጉዳዮች እንዲሁም ለአሳታሚው የሚላኩ ደብዳቤዎች ይዳሰሱ ነበር።
እ.አ.አ.1924 እስከ 1935 ዓ.ም. በነበረው እትም ጋዜጣው በዋነኛነት በወቅቱ የዓለም ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነበር። የወቅቱ የአውሮፓ
ሀገራት ግንኙነት፣ የውጭ ዜናና ፖለቲካ፣ በተለይ የኃይል አሰላለፍና የኃይል ሚዛንን የተመለከቱ ጉዳዮች በሰፊው በአዕምሮ ጋዜጣ
ይተነተኑ ነበር።
ëëë እስካሁን ካደመጣችሁት ምንባብ ምን ተረዳችሁ? ëëë
የአዕምሮ ጋዜጣ አብዛኞቹ ጽሁፎች የኢትዮጵያን አንድነት የሚሰብኩና የዘር ልዩነትንም የሚያወግዙ ነበሩ። በተለይ የኢትዮጵያ
አንድነት የተሻለ ትምህርት ለማግኘት፣ ለስልጣኔና ለዘመናዊ የኑሮ ዘይቤ ያለውን ሚና አጉልተው የሚያሣዩ ነበሩ። እ.አ.አ ከ1935
ዓ.ም. ጀምሮ በአዕምሮ ጋዜጣ ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመውረር የነበራትን ምኞት የሚያጋልጡ ጽሁፎች መታተም ጀመሩ።
አዕምሮ ጋዜጣ በመጀመሪያ በእጅ ይፃፍ ስለነበር የሥርጭት መጠኑ 24 ቅጅዎች ብቻ ነበር። እ.አ.አ. በ1929 ዓ.ም የማባዣ ማሽን
ከተገኘ በኋላ ወደ 200 ኮፒ ደርሶ እንደነበር የታሪክ ተመራማሪዎች ይገልፃሉ።
(ምንጭ፤@Team Sewasew  2021)

89 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ W9


ቅድመማዳመጥ (2 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከተማሪዎች ጋር ተወያዩ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ምንባቡን ረጋ ብለው ያንብቡላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ማንበብዎን ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቁ፤
ወዲያው ንባብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥሞና ያዳምጣሉ። ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረማዳመጥ (6 ደቂቃ)
(መ. የተከናወኑትን ተግባራት ከዓመተምህረቶቹ ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ታሪኩን ይድገሙላቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን እያዛመዱ ይሠራሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (20 ደቂቃ)


(መ. በጥንድ ሆነው በቀረቡት ዓረፍተነገሮች ውስጥ የተሰመረባቸውን ቃላት የፍቺ ልዩነት እንዲገልጹ ያድርጉ።)
[ተ. የጳውሎስ አዕምሮ በስሏል። በዕውቀት ዳብሯል ለማለት]
[ተ. ምግቡ በጣም በስሏል። እሳት ገብቶታል ለማለት]
(መ. ተስማሚ ቃል ከሳጥኑ ውስጥ መርጠው በባዶ ቦታው ላይ በማስገባት ዓረፍተነገሮቹን እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ።
እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ተስማሚ ቃላትን በባዶ ቦታው ላይ በማስገባት ዓረፍተነገሮቹን እንደገና ይጽፋሉ።]

9.1.2 አንብቦ መረዳት (25 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ያደርጋሉ።]

የማንበብ ሂደት (8 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ እንዲያነቡ ያድርጉ፤ ሁሉም ተማሪዎች ስለማንበባቸው ይከታተሉ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት በየግላቸው ድምጽ ሳያሰሙ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን ባነበቡት ታሪክ መሠረት ትክክለኛ መልስ የያዘውን መርጠው እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ
ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. መልስ ይናገራሉ፡፡ 1ሀ. 2ለ. 3መ 4ሐ]

90 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ (


ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. ቃላቱን ከተመሳሳያቸው ጋር እንዲያዛምዱ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (8 ደቂቃ)


(መ. መስተዋድዶቹን በተገቢ ቦታ ላይ በማስገባት ዓረፍተነገሮቹን እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ። ስለመስተዋድዶች በመማሪያ
መጽሐፍ ላይ የተሰጠውን ማስታወሻ መሠረት በማድረግ ያብራሩላቸው። ተጨማሪ ምሳሌዎችንም ይስጧቸው።)
[ተ. የተሰጡትን መስተዋድዶች በተገቢ ቦታ ላይ በማስገባት ዓረፍተነገሮቹን ይጽፋሉ።

9.1.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “የመጀመሪያው ጋዜጣ” የሚለውን ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው፡)
[ተ. የማዳመጥ ምንባቡ ተደግሞ ሲነበብ በጥሞና ያዳምጣሉ።]

ድኅረማዳመጥ (8 ደቂቃ)
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን ባዳመጡት ታሪክ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (8 ደቂቃ)


(መ. “ዘመን ተሻጋሪው ጋዜጠኛ” የሚለውን ታሪክ በጥንድ ሆነው አቀላጥፈው እንዲያነቡ ያድርጉ። ዕገዛ ለሚያስፈልጋቸው
ተማሪዎች ድጋፍ ይስጡ።)
[ተ. “ዘመን ተሻጋሪው ጋዜጠኛ” የሚለውን ታሪክ በጥንድ አቀላጥፈው ያነባሉ።]

መጻፍ (17 ደቂቃ)


(መ. የትምህርትቤታቸውን የአንድ ሳምንት የሥራ እንቅስቃሴ የሚገልጽ ኹለት አንቀጽ ዜና እንዲጽፉ ያድርጉ። የሐሳብ አደረጃጀቱን
በሚመለከት ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የትምህርትቤታቸውን የአንድ ሳምንት የሥራ እንቅስቃሴ የሚገልጽ ኹለት አንቀጽ ዜና ይጽፋሉ።]

9.1.4 አንብቦ መረዳት (12 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (6 ደቂቃ)


(መ. በሳምንቱ መጀመሪያ ያለውን ታሪክ በየግላቸው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው ለመረዳት ያነባሉ።]

91 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ (1


ድኅረንባብ (6 ደቂቃ)
(መ. ያነበቡትን ታሪክ መሠረት አድርገው ጥያቄዎቹን በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በቃላቸው ይመልሳሉ።]

ቃላት (20 ደቂቃ)


(መ. ዋና ቃሉንና ቅጥያዎቹን ነጣጥለው እንዲያወጡ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ.] ሀ. ልጅ -ነት -ኣቸው፣ ለ. ኢትዮጵያ -ኣዊ - ን መ. ላከ -ኣቸው
(መ. የቃላት ቢጋር ሠንጠረዡን በጋዜጣ ላይ በሚጻፉ ርዕሰጉዳዮች እንዲያሟሉ ያድርጉ።)
[ተ.] ፖለቲካዊ ጉዳዮች፣ ማስታወቂያ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣ ባህል፣ ወዘተ

የቃላት አጠቃቀም (8 ደቂቃ)


(መ. የቀረቡትን ቃላት በታሪኩ ውስጥ ያላቸውን ፍቺ እንዲጽፉ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ.] ሀ. ግልባጭ ሐ. መኮነን ሠ. ማውጣት
ለ. ጽሑፍ መ. ተስፋ ረ. አስተዋጽኦ

9.1.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (20 ደቂቃ)


(መ. በቴሌቪዢን ወይም በሬዲዮ ስላዳመጡት ዜና ርዕሰጉዳይ በቃላቸው እንዲያብራሩ ይጠይቁ። ሬዲዮና ቴሌቪዥን የማያገኙ
ተማሪዎች ካሉ ስለጋዜጠኛ ምንነትና ዋና ተግባር እንዲናገሩ ያድርጓቸው።)
[ተ. በቴሌቪዥን ወይም በሬዲዮ ያዳመጡትን ርዕሰጉዳይ በቃላቸው ያቀርባሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. “ዘመን ተሻጋሪው ጋዜጠኛ” የሚለውን ታሪክ ማጠቃለያ እንዲጽፉ ያድርጉ፤ ስለማጠቃለያ አጻጻፍ በመማሪያ መጽሐፍ
የቀረበውን ማስታወሻ ያብራሩላቸው። እንዴት ማጠቃለል እንዳለባቸው አርአያ ሆነው ያሳዩኣቸው።)
[ተ. የታሪኩን ሐሳብ አጠቃልለው ይጽፋሉ።]

9.2.1 ማዳመጥ (20 ደቂቃ) ጠያቂዋ ተማሪ

ጠያቂዋ ተማሪ የአራተኛ ክፍል ተማሪ ናት። በትምህርቷ ጎበዝ ስትሆን በስነምግባሯም የተመሰገነች ናት። ብዙ ጊዜ መጠየቅ
ትወዳለች። ዛሬ ደግሞ አባቷ ስለብዙሃን መገናኛ ምንነት እንዲነግሯት ፈልጋለች። አባቷ ስራ ውለው ሲመጡ ማስታወሻዋን ይዛ
ወደአባቷ ተጠጋች። ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ጥያቄ ልትጠይቃቸው እንደፈለገች ገለፀችላቸው። አባቷም ፈቃደኛነታቸውን
በፈገግታ አጅበው ገለፁላት።

ጠያቂዋ ተማሪ “አባዬ! የብዙሃን መገናኛን ምንነት ልትነግረኝ ትችላለህ?” አለቻቸው።

92 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ (2


አባቷም “ብዙሃኑን ማኅበረሰብ ለማግኘት የሚያስችሉ መገናኛ መንገዶች ናቸው” አሏት።

ጠያቂዋ ተማሪም “ምሳሌ ልትነግረኝ ትችላለህ አባዬ?” አለቻቸው።

አባቷም “አዎ! ሬዲዮ፣ ቴሌቪዥን፣ ጋዜጣ፣ መፅሔት ወዘተ ሁሉ የብዙሃን መገናኛ መንገዶች ናቸው” አሏት።

ëëë ጠያቂዋ ተማሪ ከዚህ ቀጥላ ምን የምትጠይቅ ይመስላችኋል? ëëë

ጠያቂዋ ተማሪ “በዓለማችን ምን ያህል የሬዲዮና የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያዎች አሉ? በኢትዮጵያስ?” ስትል ጠየቀቻቸው።

አባቷም ትንሽ አሰቡና “አይ ልጄ! በጣም ብዙ ናቸው። ለቁጥር የሚያታክቱ ናቸው። አገራችን ኢትዮጵያ አጥጋቢ ባይሆኑም ጥቂት
የሬዲዮና የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያዎች አሏት። በእነዚህም የተለያዩ መርሃግብሮች ይተላለፉባቸዋል።” በማለት ገለፁላት።

ጠያቂዋ ተማሪ አንገቷን ቀለስ አድርጋ “እሽ አባዬ በዓለማችን ስለሚኖሩ የመጽሔትና የጋዜጣ ብዛትስ የምታውቀው ይኖር ይሆን?”
በማለት ጠየቀቻቸው።

አባቷም “ይህን ያህል ብዬ ቁጥር አልነግርሽም። ግን አያሌ የመጽሔትና የጋዜጣ ህትመቶች በየቀኑ፣ በየሳምንቱ፣ በየወሩ ወዘተ
እንደሚታተሙ በእርግጠኝነት አውቃለሁ። የውጩን ተይውና የአገር ውስጡን ብንመለከት እንኳ ጥቂት የማይባሉ ህትመቶችን
እናገኛለን። ጥራታቸውንና የመረጃዎቻቸውን ትክክለኛነት ርግጠኛ ባልሆንም በቁጥር ግን አናሳ አይደሉም። ይህን ስልሽ ግን በቁጥር
አስታውሶ ለመናገር እንጅ በአገር አቀፍ ደረጃ በቂ ናቸው ማለቴ አይደለም” አሏት።

ጠያቂዋ ተማሪም “ለአንድ አገር ምን ዓይነት መገናኛ ብዙሃን፣ በምን ያህል መጠን ያስፈልጋል?” ስትል ጠየቀቻቸው።

አባቷም “አንድ አገር የጠቀስኩልሽን ሁሉንም ዓይነት የብዙሃን መገናኛ መንገዶች ሊጠቀም ይገባዋል። ከተቻለ ብዙ የቴሌቪዥንና
የሬዲዮ ማሰራጫ ጣቢያዎች በርካታ የህትመት ውጤቶች ያስፈልጋሉ”

ጠያቂዋ ተማሪ የተሰጣትን ማብራሪያ በማስታወሻዋ ላይ መዝግባ ስትጨርስ “አባዬ በጣም አመሰግንሃለሁ” አለቻቸው።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎቹ ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማዳመጥሂደት (7 ደቂቃ)
(መ. ታሪኩን ረጋ ብለው ያንብቡላቸው፤ እንዳስፈላጊነቱ ይድገሙላቸው። ከማዳመጥሂደት ጥያቄው ላይ ሲደርሱ ማንበብን
ለአፍታ ያህል ገታ አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው፤ ወዲያው ንባብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. መምህር ታሪኩን ሲያነቡ በአስተውሎት ያዳምጣሉ። ማስታወሻ ይይዛሉ።]

ድኅረማዳመጥ (10 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ባዳመጡት ታሪክ መሠረት በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ባዳመጡት ታሪክ መሠረት በቃላቸው ይመልሳሉ።]

93 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ (3


የቃላት አጠቃቀም (20 ደቂቃ)
(መ. በዓረፍተነገሮቹ የተሰመረባቸውን ቃላት በተመሳሳይ ቃላት በመተካት እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ሀ. ዘንበል ለ. ብዙ/በርካታ ሐ. ጽፋ/አስፍራ መ. ዘረዘሩላት]
(መ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በተገቢ ቃላት አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ጋዜጣ፣ መጽሔት፣ ቴሌቪዥን፣ …]

9.2.2 አንብቦ መረዳት (25 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከተማሪዎች ጋር ይወያዩ፤ እርስዎ የተማሪዎቹን ሐሳብ መቀበል እንጂ መልስ መስጠት
አይጠበቅብዎትም።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ከመምህራቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው እንዲያነቡ ያድርጉ፤ ስለማንበባቸው ይከታተሉ።)
[ተ. ታሪኩን ለመረዳት በየግላቸው በለሆሳስ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (12 ደቂቃ)


(መ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በታሪኩ መሠረት አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ። ስለአሠራሩ ድጋፍ ያድርጉላቸው። ሠርተው
ሲጨርሱ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. መቼት - ካፌ ውስጥ፣ ገጸባህርይ- ጋዜጣ አዟሪ፣ ስራአስኪያጅና አስተናጅ፣ ችግር- የብርጭቆው መሰበር፣ የድርጊቶች ቅደም
ተከተል- የጋዜጣው መበተን፣ ጋዜጣ አዟሪው ጠረጴዛውን መግፋቱ፣ የብርጭቆው መውደቅና መሰበር፣ የአስተናጋጁና
የጋዜጣ አዟሪው ግጭት፣ ስራአስኪያጁ መጥተው አስተናጋጁን መገልመጣቸው፤ የመጨረሻው ውጤት- ጋዜጣ አዟሪው
በይቅርታ መታለፉ። ጭብጥ - በሰዎች መካከል ሊኖር ስለሚገባው መተሳሰብና ይቅርታ ያሳያል፤ ሴራ በብርጭቆው መሰበር
ምክንያት አስተናጋጁና ጋዜጣ አዟሪው ተጣሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. መስተዋድዶቹን ለይተው እንዲያወጡ መመሪያ ይስጡ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. መስተዋድዶችን ለይተው ያወጣሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (5 ደቂቃ)


መ. (ዓረፍተነገሮቹን ከሳጥኑ ውስጥ ተስማሚ ቃል በመምረጥ እንዲያሟሉ ያድርጉ።)
[ተ. ተስማሚ ቃላትን በመምረጥ ዓረፍተነገሮቹን አሟልተው ይጽፋሉ።]

94 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ (4


9.2.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. የማዳመጥ ምንባቡን ደግመው ያንብቡላቸው።)

ድኅረማዳመጥ (8 ደቂቃ)
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በቃል እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በቃል ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ጋዜጣ አዟሪው” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ መሠረት ሦስት አንቀጽ እንዲጽፉ መመሪያ ይስጡ። አንቀጹን በማወዳደርና በማነጻፀር ስልት እንዲጽፉ
ፍንጭ ይስጧቸው።ተግባሩን በክፍለጊዜው ካላጠናቀቁ በቤታቸው አጠናቀው እንዲመጡ ያድርጉ።)
[ተ. በሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩ መሠረት አንቀጽ ይጽፋሉ።]

9.2.4 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ደግመው እንዲያነቡት ያድርጉ።)
(ተ. ሐሳቡን ለመረዳት በየግላቸው ታሪኩን ደግመው ያነባሉ።)

ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ለተሰጡት ቃላት ይበልጥ ተመሳሳያቸውን መርጠው እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. 1. ሐ 2. መ 3. ለ 4. ሀ ]

95 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ (5


የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)
(መ. በተሰጡት ቃላት ከአንድ በላይ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱ ከአንድ በላይ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

9.2.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (15 ደቂቃ)


(መ. የብዙኃን መገናኛዎች ስለሚሰጡት ጠቀሜታ በቃላቸው ንግግር እንዲያቀርቡ ይጠይቁ፤ ንግግራቸውን በመረጃ አስደግፈው
ያቅርቡ፤ በዚህ ደረጃ መናገርን የሚያዳብሩበት ይሁን።)
[ተ. ስለብዙኃን መገናኛ ጠቀሜታዎች በቃላቸው ንግግር ያቀርባሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. በሌላ አካባቢ ለሚኖር ጓደኛቸው ስለትምህርትቤታቸው አቀማመጥ የሚገልፅ ባለሦስት አንቀፅ ድርሰት እንዲፅፉ ያድርጉ።
በመጀመሪያ ሐሳብ እንዲያመነጩና ቢጋር እንዲነድፉ ያግዟቸው። ነጥቦቹ የትምህርትቤታቸውን አቀማመጥ ሊያሳይ በሚችል
የቦታ ቅደምተከተል እንዲያደራጇቸው ያድርጉ። በመቀጠልም በቢጋራቸው መሠረት ድርሰቱን እንዲጽፉ ያድርጉ። የሐሳብ
አደረጃጀታቸውን በሚመለከት ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ባለሦስት አንቀጽ ድርሰት ይጽፋሉ። የጻፉትን ለመምህራቸው ያሳያሉ።]

9.3.1 ማዳመጥ (25 ደቂቃ) ሀያትና ፀዳለ

ሀያትና ፀዳለ

ሀያትና ፀዳለ በአንዲት የገጠር ከተማ የሚኖሩ ጓደኛሞች ናቸው። የሚማሩት በአንድ ትምህርትቤት ውስጥ ነው። በእድሜም ሆነ
በክፍል ደረጃ አቻ ናቸው። ሁለቱም የመማር ፍላጎትና የማወቅ ጉጉት አላቸው። የቅርብ ጎረቤት ስለሆኑ በጋራ ሲያጠኑ ይውላሉ።
ርስበርስ ይጠያየቃሉ፤ በተለያዩ ጽንሰሐሳቦች ላይ ይከራከራሉ። በየትኛውም ርዕሰጉዳይ ላይ በቂ ግንዛቤ ሊኖራቸው እንደሚገባ
ያምናሉ። ስለሆነም በክፍል ደረጃቸው የቀረቡላቸውን ይዘቶች አንድ በአንድ ለማወቅ ጥረት ያደርጋሉ።

ወሩ ግንቦት ነው። በአራተኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ዘጠነኛው ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል። የምዕራፉ ርዕስ “ብዙሃን መገናኛ”
ስለሚል በዚህ ላይ በቂ ግንዛቤ ለመያዝ ብዙ አንብበዋል፤ ሰዎችንም ጠይቀዋል። አሁን ደግሞ በነሀያት ቤት ውስጥ ሆነው እየተወያዩ
ነው። ድንገት ውይይታቸው ወደክርክር ተቀየረ። የመከራከሪያ ርዕሳቸውም “ከሬዲዮና ከቴሌቪዥን ለማህበረሰቡ የበለጠ ጠቃሚ
የትኛው ነው?” የሚል ነው።

ëëë እናንተ “ከሬዲዮና ከቴሌቪዥን የበለጠ ጠቃሚው የቱ ይመስላችኋል? ëëë

ሀያት ቴሌቪዥን ከሬዲዮ የበለጠ ጠቃሚ ነው የሚል አቋም ይዛለች፤ ፀዳለ ደግሞ ከዚህ በተቃራኒ ቆማለች። ሁለቱም ሲከራከሩ
የክርክር መመሪያ ይጠብቃሉ። አንዷ ስትናገር ሌላኛዋ ታዳምጣለች፤ እንጅ አይደራረቡም።

ሀያት ወደ ፀዳለ እያየች “ቴሌቪዥን ከሬዲዮ ይበልጥ የሚጠቅመው ድምፅን ከምስል ጋር አቀናጅቶ ስለሚያቀርብ ነው። በዚህም
ለአድማጭም ሆነ ለተመልካች ሊተላለፍ የተፈለገው መልዕክት ግልፅ የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። ሳቢነቱም ቢሆን ከፍተኛ ነው” አለች።

96 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ (6


ፀዳለ ጓደኛዋ ንግግሯን ማጠናቀቋን ስታረጋግጥ መናገር ጀመረች። “ምንም እንኳ ሬዲዮ እንደቴሌቪዝን ከምስል ጋር ባያቀናጅም
መልዕክቱን ግን በአግባቡ ለማስተላለፍ ያስችላል። የሬዲዮ ቋንቋ ያለምስል ራሱን ችሎ መረጃውን በትክክል እንዲገልፅ አድርጎ
ማቅረብ ይቻላል። ደግሞስ ለአብዛኛው ማህበረሰብ ተደራሽ የሚሆነው የትኛው ነው? ሬዲዮ አይደለም እንዴ? እስኪ ገጠር ያሉትን
ዘመዶቻችንን አናስታውሳቸው። ኧረ ከተማ ውስጥም ያሉትን ምስኪኖች ተመልከቺ። አመዛኙ ሬዲዮ ተጠቃሚ ነው። ስለሆነም
ለማኅበረሰባችን የበለጠ የሚበጀው ከቴሌቪዥን ይልቅ ሬዲዮ ነው” በማለት ሰፋ ያለማብራሪያ ሰጠች።

በክርክራቸው ተመስጠው ሳለ የትምህርትቤት መግቢያ ሰዓት ደረሰባቸው። ክርክራቸውን ሌላ ጊዜ እንደሚጨርሱት ተነጋግረው


እየተቻኮሉ ወደትምህርትቤታቸው አመሩ።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ያደርጋሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. የሚከተለውን ታሪክ ረጋ ብለው ያንብቡላቸው፤ የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ማንበብዎን ለአፍታ ያህል ቆም አድርገው
ጥያቄውን ይጠይቋቸው፤ ወዲያው ንባቡን ይቀጥሉ።)
[ተ. የማዳመጥ ታሪኩን በጥሞና ያዳምጣሉ። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄውን ይመልሳሉ።]

ድኅረማዳመጥ (12 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ባዳመጡት ታሪክ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ፤
ተግባሩን ሲሰሩ ምንባቡን ደግመው ሊያነቡላቸውም ይችላሉ)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ባዳመጡት ታሪክ መሠረት በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. በዓረፍተነገሮቹ ለተሰመረባቸው ቃላት ተመሳሳይ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ።)
[ተ. ሀ. እኩል ለ. ፍላጎት ሐ. የሚጠቅመው መ. ደሃዎች]
(መ. በ “ሀ” ክፍል ለቀረቡት ቃላት ከ “ለ” ክፍል ተመሳሳያቸውን በመምረጥ እንዲያዛምዱ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. ቃላቱን ከተመሳሳያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

9.3.2 አንብቦ መረዳት (25 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

97 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ (7


የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
(መ. ታሪኩን በለሆሳስ እንዲያነቡ መመሪያ ይስጡ፤ ክትትል ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በለሆሳስ በየግላቸው ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (13 ደቂቃ)


(መ. ትክክለኛውን መልስ የያዘውን በመምረጥ የድኅረንባብ ጥያቄዎችን እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ
ይስጡ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በመምረጥ ይመልሳሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. ዋናውን ቃልና ቅጥያዎቹን በማጣመር አዲስ ቃል እንዲመሠርቱ መመሪያ ይስጡ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ዋናውን ቃልና ቅጥያዎቹን በማጣመር ቃል ይመሠርታሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. ለተሰመረባቸው ቃላት ተመሳሳይ ቃል ተክተው እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. በዓረፍተነገሮቹ ውስጥ የተሰመረባቸውን ቃላት በተስማሚ ቃላት ይተካሉ።]

9.3.3 ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. የማዳመጥ ታሪኩን ደግመው ያንብቡላቸው፤)

ድኅረማዳመጥ (8 ደቂቃ)
(መ. ባዳመጡት ታሪክ መሠረት የሐሳብ ማደራጃ ቢጋር እንዲያሟሉ ያድርጉ።)
[ተ. የማዳመጥ ታሪኩን መሠረት አድርገው የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን ያሟላሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ጋዜጠኛዋ” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

መጻፍ (15 ደቂቃ)


(መ. በቀረቡት ዝርዝር ነጥቦች መነሻነት “ጋዜጠኛዋ” የሚለውን ታሪክ ዋናሐሳብ በአንድ አንቀጽ አጠቃለው እንዲጽፉ ያድርጉ።
የተማሯቸውን መሸጋገሪያ ቃላትና ሐረጋት መጠቀማቸውን ይፈትሹ።)
[ተ. “ጋዜጠኛዋ” የሚለውን ታሪክ ዋና ሐሳብ አጠቃለው ይጽፋሉ።]

98 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ (8


9.3.4 አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ድምጻቸውን ሳያሰሙ ታሪኩን ደግመው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን ደግመው በየግላቸው በለሆሳስ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. የድህረንባብ ጥያቄዎች በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ)
[ተ. የድህረንባብ ጥያቄዎችን በቃላቸው ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ለተሰጡት ቃላት በምሳሌው መሠረት ከአንድ በላይ ፍቺ በየራሳቸው እንዲሰጡ ያድርጉ።)
[ተ. ለቃላቱ ከአንድ በላይ ፍቺ ይሰጣሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላት ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ያድርጉ፤ ግብረመልስም ይስጡ።)
[ተ. በቃላቱ ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።]

9.3.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (15 ደቂቃ)


(መ. “ከቴሌቪዥን ሬዲዮ ይሻላል” የሚለውን ሐሳብ ተቃውመው ወይም ደግፈው እንዲከራከሩ ያድርጉ። ሲከራከሩ የክርክር
መመሪያን እንዲከተሉ ያስታውሷቸው። ይህ ክፍል የመናገር ክሂል የሚያዳብሩበት ስለሆነ እያንዳንዳቸው እንዲናገሩ
ያበረታቱ።)
[ተ. “ከቴሌቪዥን ሬዲዮ ይሻላል” የሚለውን ሐሳብ በመደገፍ ወይም በመቃወም ክርክር ያደርጋሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላት ዓረፍተነገር እንዲሰሩ ያድርጉ።)
[ተ. በተሰጡት ቃላት ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]
(መ. የትናንት ውሏቸውን የሚገልጽ ዘገባ በጊዜ ቅደም ተከተል እንዲጽፉ ያድርጓቸው። በቅድሚያ ትናንት ያከናወኗቸውን ድርጊቶች
በጊዜ ቅደምተከተል እንዲዘረዝሩ ያድርጉ፡፡)
[ተ. የትናንተ ውሏቸውን በሚመለከት ዘገባ ጽፈው ያቀርባሉ።]

99 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ብዙኃን መገናኛ (9


ምዕራፍ ንግድ
10

የምዕራፉ ዓላማዎች

ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-


ƒƒ ምንባቦችን አዳምጠው በቡድን ይወያያሉ፤
ƒƒ የቀረበውን ጽሑፍ አንብበው የእያንዳንዱን አንቀፅ ዋና ሐሳብ ይለያሉ፤
ƒƒ በተሰጣቸው ርዕሰጉዳይ ላይ አጭር አንቀጽ ይጽፋሉ፤
ƒƒ ከአንድ በላይ ፍቺ ያላቸውን ቃላት ይፈልጋሉ፤
ƒƒ ቅጥያ የያዙ ቃላትን በመጠቀም አረፍተነገር ይመሠርታሉ።

10.1.1 ማዳመጥ (25 ደቂቃ) ሲራራ ነጋዴ

ሲራራ ነጋዴ

አያቴን በአካል አላውቃቸውም። ከመወለዴ በፊት ነው በዘጠና ዓመታቸው ያረፉት። በሀብት የተምነሸነሹ ሲራራ ነጋዴ እንደነበሩ
ሰምቻለሁ። የገንዘባቸውን ልክ፣ የሀብታቸውን መጠን አያውቁትም ነበር ይባላል። የሚኖሩት አንዳቤት ውስጥ ነበር። የንግድ
ሥራቸውን የሚያከናውኑት መኪና ስለማይገኝ በበቅሎ እየጫኑ ነበር። ታዲያ ወደአዲስአበባ የሚሄዱት ከአስራ ዐምስት ያላነሱ
በቅሎዎችን ይዘው ነበር። በተመሳሳይ ጓደኞቻቸውም እንዲሁ በቅሎዎችን ይዘው በአንድነት ይጓዙ ነበር። ከአሥር ቀናት አድካሚ
የእግር ጉዞ በኋላ አዲስ አበባ ይደርሱና የሚፈልጉትን መሸመት ይጀምራሉ።

ከአዲስ አበባ የሚመለሱት አንድ ወር ያህል ቆይተው ነው። በርካታዎቹ ቀናት ለጉዞ ይውላሉ፤ ጥቂቶቹን ደግሞ ተዘዋውሮ ለመሸመት
ያውሉታል። አያቴ አብዛኛውን ጊዜ አሞሌ ጨው፣ ዝሃና ሌሎች ሸቀጣ ሸቀጦችን ያመጣሉ። አያቴ የተመለሱ ቀን ቤተዘመዱ ሁሉ
“እንኳን በደህና ገባችሁ!” ለማለት ይሰበሰባል። በእድሜ የሚያንሱት የአያቴን ጉልበት በመሳም አክብሮታቸውን ይገልፁ ነበር።
ትልልቆቹን ደግሞ አያቴ ዝቅ ብለው ሰላምታ ይሰጧቸው ነበር። ታዲያ ይህን ስሰማ ያን ሁሉ ፍቅርና አክብሮት ወዴት ሰደድነው
እላለሁ።

ëëë ከዚህ ቀጥሎ ሲራራ ነጋዴው ምን የሚያደርጉ ይመስላችኋል? ëëë

100 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )


እናማ አያቴ ጭነው ያመጡት አሞሌና ሸቀጣ ሸቀጥ ከበቅሎቹ ይራገፋል። ከዚያም ከመኖሪያ ቤታቸው ጋር ተያይዛ በተሰራችና
እንደሱቅ በምታገለግለው ክፍል ውስጥ ይቀመጣል። የአያቴን መመለስ ያወቁ ሰዎች ሸቀጦችን ለመግዛት ማልደው ይመጣሉ። በጣም
ብዙ ሸማች ስለሚመጣ ወረፋ የሚያስይዝ ሰው አያቴ ይመድቡ ነበር።

አያቴ የእያንዳንዱን ሸቀጥ ዋጋ ዝርዝር ካሳወቁ በኋላ አባቴ እንዲሸጥ ያደርጉ ነበር። አባቴ ለአያቶቼ የመጀመሪያ ልጅ ስለሆነ ትልቅ
ኃላፊነት ተሰጥቶት ነበር። ሸቀጡን ይሸጣል፤ ገንዘቡን ለአባቱ ገቢ ያደርጋል። በቤት ውስጥና ከቤት ውጭ ያለንብረት ይቆጣጠራል።
የራሱን ጎጆ እስኪቀልስ ድረስ በዚህ መልኩ ወላጆቹን ያገለግል ነበር። ይኸው እስከዛሬ ድረስ አባቴ የአደገበትን የንግድ ሥራ
ተከትሏል። በርካታ ሀብትና ንብረትም አፍርቷል። አንዳቤት ወረዳ ውስጥ ከሚኖሩ ስመጥር ሀብታሞች መካከል አንዱ ለመሆን
በቅቷል።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በድኅረማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ተወያይተው ይመልሳሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


መ. (የሚከተለውን ታሪክ ረጋ ብለው ያንብቡላቸው፤ አስፈላጊ ከሆነ ይድገሙላቸው። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ
ማንበብዎን ለአፍታ ያህል ቆም አድርገው ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. ታሪኩ ሲነበብ በጥሞና ያዳምጣሉ፤ የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ይመልሳሉ።]

ድኅረማዳመጥ (15 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን ባዳመጡት ታሪክ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ባዳመጡት ታሪክ መሠረት የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


መ. (የተሰጡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር እንዲሠሩ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. በቃላቱ አውዳዊ ፍቺ እንዲሰጡ አድርገው ዓረፍተነገር ይሠራሉ።]

10.1.2 አንብቦ መረዳት (25 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ ያድርጉ፤ ሐሳባቸውንም ይቀበሉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (10ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን በለሆሳስ እንዲያነቡ ያድርጉ፤ ሁሉም ተማሪዎች እያነበቡ ስለመሆናቸው ያረጋግጡ።)
[ተ. የቀረበውን ታሪክ በለሆሳስ በየግላቸው ያነባሉ፤ ዋና ሐሳቡን ይረዳሉ።]

101 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )1


ድኅረንባብ (12 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. አብረው የሚሄዱ ቃላትን መርጠው እንዲያዛምዱ ያድርጉ። ምሳሌ ሠርተው ያሳዩአቸው።)
[ተ. አብረው የሚሄዱ ቃላትን ያዛምዳሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. የተሰመረባቸውን ቃላትና ሐረጋት አውዳዊ ፍቺ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ለተሰመረባቸው ቃላትና ሐረጋት አውዳዊ ፍቺ ይሰጣሉ።]
[ሀ. ወደር- አቻ ሐ. ለዕለት ትርፍ- ለጊዜያዊ ጥቅም
ለ. ለማታለል- ለማጭበርበር፤ መ. ምጣኔ -ልኬት]

10.1.3 ማዳመጥ (10 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ)


(መ. “ሲራራ ነጋዴ” የሚለው ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው)

ድኅረማዳመጥ (5 ደቂቃ)
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ስኬት በጥረት” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ መመሪያ ይስጡ።
ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው እገዛ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. “ነጋዴ ብሆን” በሚል ርዕስ ሦስት አንቀጽ ያለው ድርሰት እንዲጽፉ ያድርጉ። አንድ የንግድ ዘርፍ መርጠው ሐሳብ እንዲያፈልቁ፣
ቢጋር እንዲያዘጋጁና ረቂቅ እንዲጽፉ ያግዟቸው። የመጨረሻ ጽሑፋቸውንም በተመለከተ ግብረመልስ ይስጧቸው። ተግባሩ
በሰዓቱ ካላለቀ በቤታቸው እንዲያጠናቅቁ ያድርጉ።)
[ተ. “ነጋዴ ብሆን” በሚል ርዕስ ሦስት አንቀጽ ያለው ድርሰት ይጽፋሉ።]

102 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )2


10.1.4 አንብቦ መረዳት (10 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (5 ደቂቃ)


(መ. “ስኬት በጥረት” የሚለውን ታሪክ ለመረዳት በለሆሳስ እንዲያነቡ ያድርጉ)
[ተ. የታሪኩን ዋና ሐሳብ ለመረዳት በየግላቸው በለሆሳስ ያነባሉ።]

ድኅረንባብ (5 ደቂቃ)
(መ. ጥያቄዎቹን ባነበቡት ታሪክ መሠረት “እውነት” ወይም “ሀሰት” በማለት እንዲመልሱ ያድርጉ፤ ለመልሳቸው ምክንያት
እንዲሰጡ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎችን እውነት ወይም ሀሰት በማለት በማስረጃ ይመልሳሉ።]

ቃላት (15 ደቂቃ)


(መ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በደብተራቸው ላይ ሠርተው ቃላቱን የጓሮ አትክልትና ቅመማቅመም በሚሉ ርዕሶች ሥር እንዲመድቡ
መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በደብተራቸው አዘጋጅተው ቃላቱን በየወገናቸው ይመድባሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. ከሳጥኑ ውስጥ ተስማሚ ቃላት በመምረጥ ዓረፍተነገሮቹን አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ተስማሚ ቃላት በመምረጥ ዓረፍተነገሮቹን አሟልተው ይጽፋሉ።]

10.1.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (20 ደቂቃ)


(መ. ለማህበረሰቡ ከንግድ ይልቅ ግብርና ጠቃሚ ነው የሚለውን ሐሳብ በመደገፍና በመቃወም እንዲከራከሩ ያድርጉ። የክርክር
መመሪያዎችን ያስታውሷቸው።)
[ተ. ለማህበረሰቡ ከንግድ ይልቅ ግብርና ጠቃሚ ነው የሚለውን ሐሳብ በመደገፍና በመቃወም ይከራከራሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን መነሻ ሐሳቦች በማስፋፋት ሦስት አንቀጽ ያለው ድርሰት እንዲጽፉ ያድርጉ። መነሻ ሐሳቡን በማብራራትና አያያዥ
ቃላትን በመጠቀም እንዲጽፉ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. መነሻ ሐሳቦቹን መሠረት አድርገው ሦስት አንቀጽ ያለው ድርሰት ይጽፋሉ።]

103 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )3


[ተ. የተወለደችው ገጠር ነው። ትምርህቷን እንደጨረሰች የመንግስት ሥራ በመፈለግ ጊዜ አላጠፋችም። ብዙ ካሰላሰለች በኋላ
አንድ ሐሳብ መጣላት። በግል ሥራ ብትሰማራ ውጤታማ እንደምትሆን ተረዳች።
ትንሽ ገንዘብ ይዛ ወደከተማ ገባች። ወደመሃል ከተማው ቀረብ ብላ አንድ ኮንቴነር ተከራየች። ወዲያው በያዘቻት ትንሽ ገንዘብ
ዋናዋና ቁሳቁሶችን ገዛችና የጀበና ቡና ጀመረች። ብዙም ሰው የማያውቃት የገጠሯ ልጅ ጥቂት ደንበኞች ብቻ ነበሯት። እየዋለ
እያደረ ግን ደንበኞቿ በዙ።
ገቢዋም ከዕለት ወደዕለት አደገ። የሰራቻትን እያጠራቀመች ዕቁብ መጣል ጀመረች። በአጭር ጊዜ ጠርቀም ያለ ገንዘብ ደረሳት።
አንድም ብር አላጠፋችም፤ ቦታ ገዝታ ቤት ሰራችበት። የቤት እቃዋን አሟልታ ከጀበና ቡና ወደምግብ ቤት ተሸጋገረች፡]

10.2.1 ማዳመጥ (25 ደቂቃ) ህግና ንግድ

ህግና ንግድ

የንግድ ሥራ ለመሥራት የንግድ ፈቃድ ማውጣት የአስፈላጊ ነው። የንግድ ፈቃድ በአንድ የንግድ ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችልና
ሕጋዊ ከለላ የሚያጎናጽፍ ነው። ሰዎች በሚፈልጉት የሥራ መስክ ያለሥጋት መሥራት የሚችሉት ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ሲኖራቸው
ብቻ ነው።

ይሁን እንጅ አንዳንድ ሰዎች የንግድ ፈቃድ ሳያወጡ የንግድ ሥራ መስራት ይፈልጋሉ። እነዚህ ሰዎች ፈቃድ የላቸውምና ህጋዊ
አይደሉም። የንግድ ፈቃድ ሳያወጡ መስራትም ወንጀል ነው። የመንግስትን የገቢ መጠን ያሳጣል፤ የአገርንም እድገት ያዳክማል።
ቁጥጥርና ክትትል ለማድረግም ምቹ አይሆንም። ግለሰቦች ፈቃድ ከሌላቸው የስራቸው ቀጣይነት አስተማማኝ አይሆንም። ህጋዊ
አለመሆናቸው ከተደረሰበት ድርጅታቸው እንደሚዘጋ ያውቃሉና ሁልጊዜ በስጋት ውስጥ ይኖራሉ። በስጋት ውስጥ ሆኖ መስራት
ደግሞ በሥራ ውጤታማ አያደርግም።

የንግድ ፈቃድ የያዙ ሰዎች ግን ያለምንም ሥጋት መሥራት ይችላሉ። ህጋዊ ስለሆኑ መብቶቻቸውን የመጠየቅና የማስከበር እድል
አላቸው። ማንኛውንም የንግድ ሥራ ሕጋዊ ፈቃድ ይዞ መሥራት ለንግድ አሠራር ሥርዓት የራሱ ድርሻ አለው። ፈቃድ ይዞ
መሥራት ለሕግ ተገዢ መሆንንም ያሳያል። ተገቢውን ግብር በወቅቱ በመክፈል ለአገር እድገት የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ
ይሆናል። ምክንያቱም በግብር የሚሰበሰበው ገንዘብ እንደመንገድ፣ መብራት፣ ውሃ የመሳሰሉትን መሠረተልማቶች ለማሟላት
ያስችላል። የትምህርት ተቋማትን በማስፋፋት ዜጎችን ለማስተማር ይረዳል። የጤና ተቋማትንም በማስፋፋት ተገቢ የጤና
አገልግሎት ለመፍጠርም ያስችላል።

ስለሆነም በንግድ ዘርፍ የሚሰማሩ ሰዎች ህጋዊ ፈቃድ ማውጣት ይኖርባቸዋል። ያለፈቃድ የሚሰሩ ሰዎችን መምከርና መገሰፅ
አስፈላጊ ነው። ግብር እየከፈሉ መስራት ጠቃሚ መሆኑን ማስተማር ያስፈልጋል። ህጋዊ ሆነው ተገቢ ግብር ለመክፈልም
ገቢያቸውንና ወጪያቸውን ለገቢዎች ጽህፈትቤት ማሳወቅ ይኖርባቸዋል። እንዲህ ያለው መረጃ ግብርን በገቢያቸው መጠን ብቻ
አስልቶ ለመጣል ያስችላል። በዚህም ነጋዴዎች ያልተጋነነና ትክክለኛ የግብር መጠን እንዲከፍሉ ያግዛቸዋል።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ከመምህር ጋር እንዲወያዩ ያድርጉ፤ መልሳቸውን ይቀበሉ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ያደርጋሉ።]

104 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )4


የማዳመጥ ሂደት (9 ደቂቃ)
(መ. ምንባቡን ረጋ ብለው ያንብቡላቸው፤ የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ላይ ሲደርሱ ንባቡን ለአፍታ ገታ አድርገው ጥያቄውን
ይጠይቋቸው፤ ወዲያው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
[ተ. ታሪኩ ሲነበብ በአስተውሎት ያዳምጣሉ፤ የማዳመጥ ሂደት ጥያቄውን ይመልሳሉ።]

ድኅረማዳመጥ (13 ደቂቃ)


(መ. ህጋዊና ህገወጥ ንግድን በሚገለጹ መረጃዎች የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን እንዲሞሉ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. ስለህጋዊና ህገወጥ ንግድ ምንነት፣ ጥቅምና ጉዳት ባዳመጡት መሠረት ቢጋሩን ያሟላሉ]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን ቃላት ከተቃራኒያቸው ጋር እንዲያዛምዱ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን ከተቃራኒያቸው ጋር ያዛምዳሉ።]

10.2.2 አንብቦ መረዳት (25 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ርስበርሳቸው እንዲወያዩ ያድርጉ።)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. “አተርፍ ባይ አጉዳይ” የሚለውን ታሪክ ድምጽ ሳያሰሙ ደግመው እንዲያነቡ ያድርጉ)
[ተ. ታሪኩን በለሆሳስ ደግመው በማንበብ ይከልሳሉ።]

ድኅረንባብ (12 ደቂቃ)


(መ. በድኅረንባብ የቀረቡትን ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ በመምረጥ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ.] መ. ለ. ለ.]

ቃላት (7 ደቂቃ)
(መ. በተሰጡት ቃላት አውዳዊ ፍቺ እንዲኖራቸው አድርገው ዓረፍተነገር እንዲሰሩ ያድርጉ። ምሳሌ ሠርተው ያሳዩአቸው።)
[ተ. በቃላቱ ዓውዳዊ ፍቺ እንዲያሳዩ አድርገው ዓረፍተነገር ይመሠርታሉ።
ምሳሌ፡- በበዓል ሰሞን ወደገበያ የሚወጣው ሸማች በርካታ ነው።

105 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )5


የቃላት አጠቃቀም (8 ደቂቃ)
(መ. የቀረቡት ፈሊጣዊ አባባሎች ፍቺ በጽሑፍ እንዲገልጹ ያድርጉ፤ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. ሀ. አላፊ ጠፊ ለ. ህገወጥ ንግድ ሐ. በሽተኛ ሆኖ መኖር መ. ደብዛው የጠፋ]

10.2.3 ማዳመጥ (10 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ)


(መ. “ህግና ንግድ” የሚለውን ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው።)

ድኅረማዳመጥ (5 ደቂቃ)
(መ. ባዳመጡት ታሪክ መሠረት የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ሀ. ፈቃድ የሌለው ንግድ በመንግስት ያልተመዘገበ ስለሆነ መንግስት ማግኘት ያለበትን ግብር እንዳይሰበስብ ያደርገዋል።]
ለ. ግብር ባለመክፈላቸው ከዛሬ ነገ መንግስት ያዘን ፤ ወይም ንብረታችን ተወረሰ፤ ወይም ታሰርን እያሉ ስለሚጨነቁ ነው።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “አተርፍ ባይ አጉዳይ” የሚለውን ታሪክ በየግላቸው በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ። ሦስተኛ
ክፍል የተቀመጠውን የአቀላጥፎ ማንበብ መመዘኛ ብልሃት ተጠቅመው ምዘና ያካሂዱ። የምዘና ውጤቱን ለክፍል ደረጃው
ከተቀመጠው ሰታንዳርድ ጋር ያነፃፅሩ። ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ተማሪዎች ለይተው ድጋፍ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በየግላቸው በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. በጥንድ ሆነው ሐሳብ እያዋጡ ህጋዊ ነጋዴ የሚያሰኙ ጉዳዮችን የሚገልፅ ባለኹለት አንቀጽ ድርሰት እንዲጽፉ ያድርጓቸው።
ተማሪዎቹ አንዳንድ አረፍተነገር እየተቀባበሉ ተራበተራ እንዲጽፉ መመሪያ ይስጧቸው።)
[ተ. በጥንድ ሆነው ሐሳብ እያዋጡ ህጋዊ ነጋዴ የሚያሰኙ ጉዳዮችን የሚገልፅ ባለኹለት አንቀጽ ድርሰት ይጽፋሉ።]

10.2.4 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (8 ደቂቃ)


መ. (“አተርፍ ባይ አጉዳይ” የሚለውን ታሪክ ለመረዳት ደግመው እንዲያነቡ ያድርጉ።)

ድኅረንባብ (12 ደቂቃ)


(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
[ተ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

106 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )6


ቃላት (10 ደቂቃ)
መ. (ለቀረቡት ብያኔዎች የሚስማማ ቃል ወይም ሐረግ ከታሪኩ ሦስተኛ አንቀጽ ውስጥ እንዲፈልጉ ያድርጉ። መልሱን ከሥር
ይመልከቱ።)
[ተ.] ሀ. [በዋስትና ሰጥተው] ሐ. [ያለደረሰኝ] ሠ. [የውኃ ሽታ ሆነ]
ለ. [መካዘን] መ. [ቀብድ]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. ለተሰመረባቸው ቃላት ተመሳሳይ ቃል ከሳጥኑ እየመረጡ እንዲተኩ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. የተሰመረባቸውን ቃላት በተመሳሳይ ቃላት ተክተው ዓረፍተነገሩን ይጽፋሉ።]

10.2.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (15 ደቂቃ)


(መ. አንድ ሰው አብረን እንነግድ ብሎ ገንዘብ ቢጠይቃቸው ምን እንደሚያደርጉ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩ ያድርጓቸው።)
[ተ. በተሰጠው ርዕስ ላይ ከጓደኞቻቸው ጋር ውይይት ያደርጋሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. ጅምር አንቀጹን መነሻ በማድረግ ኹለት አንቀጽ ያለው አጭር ድርሰት እንዲጽፉ ያድርጉ)
[ተ. ጅምር አንቀጹን አሟልተው ባለኹለት አንቀጽ ድርሰት ይጽፋሉ።]

10.3.1 ማዳመጥ (25 ደቂቃ) የኹለት ዓለም ነጋዴዎች

የኹለት ዓለም ነጋዴዎች

አቶ መስፍን መካከለኛ ገቢ ካላቸው ነጋዴዎች መካከል አንዱ ናቸው። ከገበያው በስተምስራቅ አቅጣጫ የሸቀጣሸቀጥ ሱቅ አላቸው።
በአቅራቢያቸው ወደሚገኝ ትልቅ ከተማ እየሄዱ ሸቀጦችን በመኪና ጭነው ያመጣሉ። ባልተጋነነ ትርፍ ለማኅበረሰቡ ይሸጣሉ።
የአካባቢው ሰው በአዘቦት ቀን ሳይቀር በሰልፍ የሚፈልገውን ነገር ሲገዛ ይውላል። ተጎራብተዋቸው ያሉ ነጋዴዎች ግን በየሸቀጦቹ
የሚጨምሩት ዋጋ ከፍ ያለ ነበር። ስለሆነም ብዙ ሰው ከነሱ ይልቅ ከአቶ መስፍን መግዛትን ይመርጣል። ከነሱ ይጠይቃል፣ ከአቶ
መስፍን ይገዛል።

ጎረቤቶቻቸው ያላግባብ በሸቀጦች ላይ ዋጋ እንዲጨምሩ አቶ መስፍንን ወተወቷቸው፤ ቆይተውም ተቀየሟቸው። እርሳቸው ግን ተገቢ
ያልሆነ ትርፍ ማግበስበስ እንደማይሹ ተናገሩ። ያላግባብ የተሰበሰበ ገንዘብም እንደማይባረክላቸው ገለጹ። ይልቁንም ጎረቤቶቻቸው
ዋጋ እንዲያስተካክሉ አሳሰቧቸው። የንግድ ሥራ ቀስበቀስ የሚታደግበት እንጅ በአቋራጭ የሚከበርበት አለመሆኑን አስረዷቸው።
ጎረቤቶቻቸው ግን የአቶ መስፍንን ምክር እንደንቀት ቆጠሩት። ሰደቧቸው፤ ዛቱባቸው። ሊበቀሏቸውም ቀን ይቆጥሩላቸው
ጀመር። አቶ መስፍን ግን ዛቻውን ከእቁብ ሳይቆጥሩ ሥራቸውን መሥራት ቀጠሉ። በርካታ ደንበኞቻቸው ይህንን ስለሰሙ መከታ
እንደሚሆኑላቸው ቃል ገቡላቸው።

107 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )7


ከእለታት አንድ ቀን የአቶ መስፍን ሱቅ በሌሊት በሌቦች መሰርሰር ይጀምራል። ሆኖም ሌቦቹ በአካባቢው ማኅበረሰብ እጅ ከፍንጅ
ተያዙ፤ በብርሃን ሲታዩ እነዚያ ጎረቤቶቻቸው ነበሩ። በህግ ቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ተደረገ። በአቃቤ ህግ ክስ ተመሥርቶባቸው
ለኹለት ዓመታት ጽኑ እስራት ተፈረደባቸው። ወደማረሚያቤት ወረዱ። አቶ መስፍን ግን ራሳቸውንም ማኅበረሰቡንም በሚጠቅም
መልኩ ንግዱን አጠናከሩት። ሀብታቸው እየጨመረ ስለሄደ ሱቃቸውን ወደጅምላ ማከፋፈያነት ቀየሩት። የታሰሩት ከማረሚቤት
ሲወጡ አቶ መስፍንን ይቅርታ ጠየቋቸው። አቶ መስፍንም መፀፀታቸውን አይተው ይቅርታ አደረጉላቸው። ስነምግባራቸውን
አሻሽለው የንግድ ሥራቸውን እንደገና ጀመሩ።

ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ላይ ርስበርስ እንዲወያዩ መመሪያ ይስጡ።)
[ተ. በቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች ይወያያሉ።]

የማዳመጥ ሂደት (10 ደቂቃ)


(መ. ታሪኩን ረጋ ብለው ያንብቡላቸው፤ የማዳመጥሂደት ጥያቄው ላይ ሲደርሱ ጥያቄውን ይጠይቋቸው። ወዲያው ማንበብዎን
ይቀጥሉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ታሪኩን ይድገሙላቸው።)
[ተ. የማዳመጥ ታሪኩን በአስተውሎት ያዳምጣሉ። የማዳመጥ ሂደት ጥያቄውን ይመልሳሉ።]

ድኅረማዳመጥ (12 ደቂቃ)


(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን ባዳመጡት ታሪክ መሠረት በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ድጋፍ ያድርጉ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በቃላቸው በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

የቃላት አጠቃቀም (15 ደቂቃ)


(መ. በተሰጡት ቃላትና ሐረጋት ዓረፍተነገር እንዲሰሩ ያድርጉ፤)
[ተ. ከፍተኛ ወንጀል የፈፀመ ሰው አመክሮ የሌለው ጽኑ እስራት ይፈረድበታል።]

10.3.2 አንብቦ መረዳት (25 ደቂቃ)

ቅድመንባብ (3 ደቂቃ)
(መ. በቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ ከተማሪዎች ጋር ተወያዩ። ሐሳባቸውን ይቀበሉ)
[ተ. በቅድመንባብ ጥያቄዎቹ ላይ ከመምህራቸው ጋር ይወያያሉ።]

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. ተማሪዎች ታሪኩን ድምጽ ሳያሰሙ በየግላቸው እንዲያነቡ መመሪያ ይስጡ፤ ሁሉም ተማሪዎች ስለማንበባቸው ይከታተሉ፤)

108 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )8


ድኅረንባብ (10 ደቂቃ)
(መ. የድኅረንባብ ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ፤ እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።) መልስ፡-
[ተ. ሀ. በስራ ፈጠራ የትምህርት መስክ
ለ. ያገኙትን ዕውቀት ወደተግባር ለውጦ መጠቀም ሲቻል ነው።
ሐ. ስራ እስኪገኝ ከመጠበቅ ስራ ፈጥረው እንዲሰሩ ነበር፤ እነሱ ግን ምክሩን አልሰሙም።]
መ. የታሪኩ ዋና መልዕክት ስራ በመፍጠር በራስ ጥረት መለወጥ እንደሚቻል ነው]

ቃላት (5 ደቂቃ)
(መ. ባዳመጡት ታሪክ መሠረት ለቀረቡት ቃላትና ሐረጋት ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ፤)
[ተ . ከነመረጃው፣ መቦርቦር/መፈልፈል፣ በጥቅል/በደርዘን፣]

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን ቃላትና ሐረጋት በራሳቸው አገላለጽ አብራርተው እንዲገልጹ ያድርጉ።)
[ተ. ሀ. የዶሮ/ የከብት ምግብ ሐ. የሚያስገርም ሠ. በስራ ቀን
ለ. በርከት ያለ መ. ስኬት/ ከፍተኛ ቦታ]

10.3.3 ማዳመጥ (10 ደቂቃ)

የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ)


(መ. “የኹለት ዓለም ነጋዴዎች” የሚለውን ታሪክ ደግመው ያንብቡላቸው።)

ድኅረማዳመጥ (5 ደቂቃ)
(መ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዳስፈላጊነቱ ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. የድኅረማዳመጥ ጥያቄዎችን በጽሑፍ ይመልሳሉ።]

አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)


(መ. “ዶሮ ነጋዴው” የሚለውን ታሪክ በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. ታሪኩን በጥንድ እየተቀባበሉ በትክክል፣ በፍጥነትና በተገቢ አገላለጽ ያነባሉ።]

መጻፍ (20 ደቂቃ)


(መ. ሕገወጥ ነጋዴን ለመቆጣጠር የሚወሰዱ ርምጃዎችን በሚመለከት ኹለት አንቀጽ ያለው ድርሰት ጻፉ።)
[ተ. ታሪኩን በኹለት አንቀጽ አሳጥረው ይጽፋሉ።]

109 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )9


10.3.4 አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)

የማንበብ ሂደት (7 ደቂቃ)


(መ. “ዶሮ ነጋዴው” የሚለውን ታሪክ ለመረዳት በየግላቸው እንዲያነቡ ያድርጉ።)

ድኅረንባብ (13 ደቂቃ)


(መ. ጥያቄዎቹን “እውነት” ወይም “ሀሰት” ብለው እንዲመልሱ ያድርጉ፤ ለመልሳቸው ምክንያት እንዲሰጡ ይጠይቁ።)
[ተ. የድህረንባብ ጥያቄዎቹን እውነት ወይም ሀሰት በማለት ይመልሳሉ።]

ቃላት (10 ደቂቃ)


(መ. ዋናውን ቃልና ቅጥያዎቹን በማጣመር ውስብስብ ቃላት እንዲመሠርቱ ያድርጉ።)
[ተ. ሀ. አዘጋጀሁላቸው ሐ. ተመካከሩ
ለ. ተመለስኩ መ. ተመርቄያለሁ

የቃላት አጠቃቀም (10 ደቂቃ)


(መ. የተሰጡትን ቃላት በተገቢ ቦታ ላይ በማስገባት ዓረፍተነገሩን እንደገና እንዲጽፉ ያድርጉ።)
[ተ. ቃላቱን በተገቢ ቦታቸው በማስገባት ዓረፍተነገሩን እንደገና ይጽፋሉ።]

10.3.5 ክለሳ (40 ደቂቃ)

መናገር (15 ደቂቃ)


(መ. በመንግስት ተቀጥሮ ከመስራት በግል ስራ መሰማራት ይሻላል” የሚለውን ሐሳብ በመደገፍ ወይም በመቃወም ክርክር
እንዲያካሂዱ ያድርጉ፤)
[ተ. በተሰጠው ርዕስ ላይ ክርክር ያደርጋሉ።]

መጻፍ (25 ደቂቃ)


(መ. “ዶሮ ነጋዴው” የሚለውን ታሪክ የመጨረሻ አንቀጽ ጭብጥ በራሳቸው አገላለጽ በኹለት አንቀጽ አስፋፍተው እንዲጽፉ
ያድርጉ። አንድ ሐሳብ እንዴት እንደሚስፋፋ አርዓያ ሆነው ሠርተው ያሳዩኣቸው።)
[ተ. “ዶሮ ነጋዴው” የሚለውን ታሪክ የመጨረሻ አንቀጽ ጭብጥ በኹለት አንቀጽ አስፋፍተው ይጽፋሉ።]

110 አማርኛ 4ኛ ክፍል ~ የመምህር መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 10 ንግድ )0


ዋቢ መጻሕፍት

ማረው አለሙ። (2005)። በሳል ድርሰት ማስተማሪያ። አዲስ አበባ፤ አልፋ አታሚዎች።
ባየ ይማም። (1987)። የአማርኛ ሰዋስው። ት.መ.ማ.ማ.ድ
ብርሃነ መስቀል ደጀኔ። (1987)።ዉኃ ዉኃ የሚያሰኝ ጉዞ።
ቱር ኢን ኢትዮጵያ። (ሚያዘያ 1 2019)።
አብክመ ባህልና ቱሪዝም። (ቀን የሌለው)። አማራ ክልልና መስህቦቿ።
አዲስ ዘመን ጋዜጣ። (ሰኔ 14/ 2012)።
ኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር እና አብክመ ትምህርት ቢሮ። (2007)። ስድስተኛ ክፍል አማርኛ እንደአፍመፍቻ ቋንቋ የተማሪ
መጽሐፍ።
ኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር እና አብክመ ትምህርት ቢሮ። (2006)። አራተኛ ክፍል አማርኛ እንደአፍመፍቻ ቋንቋ የመምህር
መምሪያ።
ከበደ ሚካኤል። (1999)። ታሪክና ምሣሌ። አዲስ አበባ፤ ሜጋ አሳታሚና ማከፋፈያ፡፡
ዘሪሁን አስፋው። (1992)። የሥነጽሑፍ መሠረታውያን። አዲስ አበባ፤ ንግድ ማተሚያ ድርጅት።
ደረጀ ገብሬ። (1996)። ተግባራዊ የጽሕፈት መመሪያ። አዲስ አበባ፤ ንግድ ማተሚያ ድርጅት።
ጌታሁን አማረ። (1989)። የአማርኛ ሰዋስው በቀላል አቀራረብ። አዲስ አበባ፤ አልፋ አታሚዎች።
healthline.com. (March 19, 2019). Why Is Water Important? 16 Reasons to Drink Up.
https://am.Sewasew.com/p/። (2021)። አዕምሮ የመጀመሪያው በአማርኛ ይታተም የነበረ ጋዜጣ።

111

Вам также может понравиться