Академический Документы
Профессиональный Документы
Культура Документы
የተማሪ መጽሐፍ
2ኛ ክፍል
አዘጋጆች
አርታኢ
ሙሉሰው ከበደ ሰጋሁ
ሰዓሊ
አይናዲስ አምባው ምህረቴ
ዲዛይነር
ገነት አባተ መኮንን
የቡድን መሪ
ዶር. ማረው አለሙ ተሰማ
ምዕራፍ 1 አልባሳት������������������������������������������������������������������������������������������������������������� 1
ምዕራፍ 2 ወቅቶች������������������������������������������������������������������������������������������������������������� 16
ምዕራፍ 3 ታሪኮች������������������������������������������������������������������������������������������������������������� 30
ዋቢዎች������������������������������������������������������������������������������������������������������������������������������ 150
መግቢያ
ይህ የተማሪ መጽሐፍ በፍኖተካርታውና በአገርአቀፍ ምዘናዎች ምክረሐሳቦች መሠረት በ2013 ዓ.ም
በተደረገው የሥርዐተትምህርት ለውጥ መነሻነት የተዘጋጀ ነው። በመሆኑም በመጽሐፉ ዝግጅት
የሚከተሉት ጉዳዮች ልዩ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል፤
1. የተማሪዎችን በጥልቀት የማሰብ፣ የመተንተን፣ የመጠየቅ፣ ችግር የመፍታት፣ የመወሰን፣
የመግባባትና የመገምገም ክህሎት የሚያሳድጉ ዓይነተብዙ ተግባራት ተካትተዋል፤
የተማሪ መጽሐፉ ዐቢይ ዓላማ የልጆችን በአማርኛ ቋንቋ የማዳመጥና የመናገር፣ የማንበብና የመጻፍ
ችሎታ ለማሳደግና በጥልቀት የማሰብና የመግባባት ብቃታቸውን ለማጎልበት ነው። መጽሐፉ በልጆች
የማንበብና የመጻፍ ስኬት ላይ የተሠሩ ምርምሮችን ግኝቶችና የአማርኛ ቋንቋን መሠረታዊ ባሕርያት
መነሻ አድርጎ የተዘጋጀ ነው።
የትምህርት ይዘቶቹ በአሥር ምዕራፎች የተደራጁ ናቸው፤ የመጀመሪያዎቹ ዐምስት ምዕራፎች
የትምህርት ይዘቶች በመጀመሪያው መንፈቀዓመት፣ ቀሪዎቹ ዐምስት ምዕራፎች ደግሞ በኹለተኛው
መንፈቀዓመት እንዲጠናቀቁ ሆነው የቀረቡ ናቸው። የአንድ ምዕራፍ የትምህርት ይዘቶች ደግሞ
በሦስት ሳምንታት እንዲጠናቀቁ ታስበው ነው የተደራጁት። የየምዕራፎቹ የትምህርት ይዘቶች
በአንድ ነጥብ በተለዩ ሦስት ቁጥሮች የተወከሉ ናቸው፤ የመጀመሪያው ቁጥር ምዕራፍን፣ ኹለተኛው
ቁጥር ሳምንትንና ሦስተኛው ቁጥር ቀንን የሚወክሉ ናቸው። ለምሳሌ፣ 1.1.1 የሚሉ ቁጥሮች
ምዕራፍ አንድን፣ ሳምንት አንድንና ቀን አንድን በቅደምተከተል ይወክላሉ፤ እንዲሁም 10.2.3
የሚሉ ቁጥሮች ምዕራፍ አሥርን፣ ሳምንት ኹለትንና ቀን ሦስትን በቅደምተከተል ይወክላሉ።
ታሪኮችን ይተርኩላቸው፤
በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉትን ወይም ለደራጃቸው የሚመጥኑ ሌሎች ታሪኮችን አዘውትረው
እንዲያነቡ ያበረታቷቸው፤ ለማንበብ የሚቸገሩባቸውን ቃላትና ዓረፍተነገሮች አርአያ
ሆነው በማንበብ እርስዎ እንዳነበቡት አድርገው እንዲያነቧቸው በአግባቡ ያግዟቸው፤
ማጣመር/መነጠል
ይህ ክፍል ቃላትን በማንበብና ወደተለያዩ ክፍሎች በመነጠል ወይም በማጣመር ላይ ስለሚያተኩር፣
ልጆቹ ቃላቱን እንዲያነቡና በተገቢ የፊደል አሰዳደር ሥርዓት እንዲጽፉ ያግዛቸዋል።
ማንበብ
ይህ ምልክት የሚነበቡ አዳዲስ ቃላትንና ተዘውታሪ ቃላትን፣ ዓረፍተነገሮችን፣ አጫጭር ታሪኮችን
ወይም ምንባቦችን የትምህርት ይዘቶች ያመላክታል።
መጻፍ
ይህ ምልክት ፊደላትንና ቃላትን የመጻፍ፣ እንዲሁም ሐሳብን በሥዕልና/ወይም በቃላት የመግለጽ
የትምህርት ይዘቶችን ያመላክታል፤
ቅድመማዳመጥ
የምታውቋቸውን የልብስ ዓይነቶች ዘርዝሩ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. ሹ-ራ-ብ ሐ. አ-ባ-ቷ
ለ. ቀ-ሚ-ስ መ. ል-ብ-ስ
ሀ. ጥቁር ኮት
ለ. ጥበብ ቀሚስ
ሐ. የደንብ ልብስ
መ. የበዓል ልብስ
የአክሊሉ ነጭ ሸሚዝ
አክሊሉ ነገ የልደቱ ቀን ነው። ታላቅ እህቱ በጧቱ ተነሳች። የአክሊሉን
ልብሶች ማጠብ ጀመረች። ነጩን ሸሚዝና አዲስ የተገዛውን ጥቁር ኮት
በሳፋ ውስጥ አደረገች። በኦሞና በዉኃ ዘፈዘፈቻቸው። ከጥቂት ደቂቃዎች
በኋላ ልብሶቹን በማሸት ልታጥብ ዝቅ አለች። ያየችውን ማመን አቃታት።
እናቷን ተጣራች። እናቷም ባዩት ነገር በጣም ተናደዱ። ወዲያውኑ አንድ
ሐሳብ መጣላቸው። ነጩን ሸሚዝ በሌላ ሳፋ በበረኪናና በኦሞ እንደገና
ዘፈዘፉት። ከአንድ ስዓት በኋላ አለቀለቁት። ሸሚዙ እንደድሮው ነጭ ሆነ።
እህቱና እናቱም ተቃቅፈው በደስታ ዘለሉ።
ቅድመንባብ
በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ በጥንድ ተወያዩ።
ሀ. “ህልም እልም” ከሚለው ርዕስ ምን ትገምታላችሁ?
ለ. ልብስ ለመግዛት ገንዘብ ከየት ታገኛላችሁ?
“ህልም እልም”
አንድ አርሶአደር ብዙ የወተት ላሞች ነበሩት። አንድ ቀን ለልጁ በማሰሮ የሞላ
ወተት እንድትሸጥ ሰጣት። ወተቱንም ሸጣ ጫማ፣ ቲሸርት፣ ጉርድቀሚስና
ሸራጫማ እንድትገዛ ፈቀደላት። ልጅቷም በመንገድ እየሄደች ብዙ ነገሮችን
አሰበች።
“ነገ አዲስ ልብስ ለብሼ ወደትምህርትቤት እሄዳለሁ። ከሌሎች ልጆችም
የበለጠ ቆንጆ እሆናለሁ። ልጆችም አብረን እንጫወት ይሉኛል። እኔ ግን
ፊቴን እንዲህ አድርጌ እመልስባቸዋለሁ” ብላ አንገቷን መለስ አደረገች። ከራሷ
ላይ የነበረው ማሰሮ ተንሸራቶ በመውደቁ ተሰባበረ፤ ወተቱም የመንገዱን
ጠርዝ ይዞ ቁልቁል ፈሰሰ።
የቃላት አጠቃቀም
ቃላቱን ከሥዕላዊ መግለጫዎቹ ጋር አዛምዱ።
“ሀ” “ለ”
1. ጥልፍቀሚስ ሀ.
2. ሹራብ ለ.
3. ሸሚዝ ሐ.
4. ቁምጣ መ.
5. ቲሸርት ሠ.
ቅድመማዳመጥ
ሥዕሉን ተመልከቱና ስለታሪኩ ገምቱ።
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ቃላት/ሐረግ ፍቺ ተናገሩ።
ቃላት
ሀ. ተ - ሰ - ቅ - ለ - ዋ - ል ሐ. ተ - ደ - ር - ድ - ረ - ዋ - ል
ለ. ተ - ቀ - ም - ጠ - ዋ - ል መ. ተ - ን - ጠ - ል - ጥ - ለ - ዋ - ል
አቀላጥፎ ማንበብ
“የአክሊሉ ነጭ ሸሚዝ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
1.1.4 መጻፍ
ሀ. አንገቷን ለ. ሸራ ጫማ ሐ. ፈቀደላት
ሀ. እ - ን - ድ - ት - ሸ - ጥ ሐ. ቁ - ል - ቁ - ል
ለ. እ - የ - ሄ - ደ - ች መ. እ - ን - ጫ - ወ - ት
1.1.5 ክለሳ
ቅድመማዳመጥ
በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ።
ድኅረማዳመጥ
ሀ. ባለታሪኮቹ እነማን ናቸው?
ቃላት
ለ. ጃኖ መ. የገና በዓል
ሀ. ይ-ከ-በ-ራ-ል
ለ. ተ-ጫ-ም-ታ-ለ-ች
ሐ. ኩ-ታ-ቸ-ው-ን
ተንኮለኛዋ አይጥ
አንድ ቀን አንዲት ተንኮለኛ አይጥ ከአንድ ቤት ሾልካ ገባች። ቀስ ብላ
በቁምሳጥኑ ውስጥ ተደበቀች። ፎጣውን፣ ሱሪውን፣ ጋቢውን፣ ሸሚዙን ፣
ኮቱንና ቀሚሶችን በጣጠሰቻቸው። በማግስቱ ባለቤቱ ወጥመድ አጠመደ።
አይጧ ተያዘች። ባለቤቱም ከወጥመድ በማላቀቅ ሊገላት ሲሞክር ድመቷ
እመር ብላ ያዘቻት።
ቅድመንባብ
ሥዕሉን ተመልከቱና ስለታሪኩ ገምቱ።
የልጁ መኝታቤት
ልጁ ከትምህርትቤት ሲመለስ ለመጫወት ይቸኩላል።
የደንብ ልብሱንና ቦርሳውን ባገኘበት ይጥላል። አንድ
ቀን እናቱ ወደመኝታቤት ገቡ። ቤቱ ተዝረክርኳል።
ልጁን ጠሩና “ጥፋትህን አውቀሃል?” አሉት። “አዎ
እማዬ! አሁን አስተካክላለሁ” አለ። ወዲያውኑ የደንብ
ልብሱን ካልጋው ራስጌ ባለው ቁምሳጥን አጣጥፎ ከተተ። ቦርሳውን
በመደርደሪያ ላይ አስቀመጠ። ጫማውን በአልጋው ሥር አኖረ።
(ምንጭ፤ አማርኛ እንደአፍ መፍቻ ቋንቋ ከ2ኛ የተማሪ መጽሐፍ፣ መጠነኛ ለውጥ ተደርጎ የተወሰደ)
የቃላት አጠቃቀም
በምሳሌው መሠረት በልጁ መኝታቤት የሚታዩትን አልባሳት ጻፉ።
ምሳሌ፡- ካልሲ
ቅድመማዳመጥ
የበዓላት ልብሶች መቼ መቼ የሚለበሱ ይመስላችኋል?
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. ቀኑብሽና ቤተሰቦቿ ወደየት ሄዱ?
ለ. የቀኑብሽ እናት “የፈራሁት አልቀረም” ያሉት ለምን ይመስላችኋል?
ቃላት
1.2.4 መጻፍ
ሀ. የ-ጥ-ል-ፍ-ቀ-ሚ-ስ ሐ. የ-ሴ-ት-ጫ-ማ
ለ. የ-አ-ን-ገ-ት-ል-ብ-ስ መ. የ-ጃ-ኖ-ጥ-ለ-ት-ኩ-ታ
ሀ ለ ሐ መ
3. ቃላቱን ወይም ፊደላቱን በመግድፍና ቦታ በመቀያየር ሌሎች ቃላት
መሥርቱ።
ምሳሌ፡- ቁምሳጥን
1.2.5 ክለሳ
የጥጥ
ነጭ
ልብስ
ቅድመማዳመጥ
በወላጆች ቀን፣ በትምህርትቤት መከፈቻ ቀን ወይም በሽልማት ሥርዓት
ምን ዓይነት ልብሶችን ትለብሳላችሁ? ለምን?
ቃላት
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
“ታጥቦ ጭቃ”
በአንድ ግቢ ውስጥ ሰው፣ ውሻና አህያ ይኖሩ ነበር። ሰውዬው ልብስ አጣቢ
ነው። አንድ ቀን የወለል ምንጣፍ፣ ብርድልብስ፣ በርካታ መጋረጃዎች፣
ስጋጃና የተለያዩ አልባሳትን በመያዝ ወደወንዝ ወርዶ ሲያጥብ ዋለ።
በመጨረሻ በአህያው ያልደረቁ ልብሶችን ጭኖ ወደቤት ተመለሰ። ውሻው
እርቦት ስለነበር እጥፍጥፍ ብሎ ተኛ። አህያው ጭነቱ እስከሚወርድለት
በአጥሩ ጥግ ቆመ። ሰውዬው ልብሶቹን አውርዶ በልብስ ማስጫ ገመዱ ላይ
ካሰጣ በኋላ ወደመኝታቤቱ ገብቶ ተኛ።
ቅድመንባብ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች በቃል መልሱ።
ሀ. ሥዕሉንና ርዕሱን በማስተዋል ስለታሪኩ ገምቱ?
ለ. “የቸኮለ አፍሶ ለቀመ” ማለት ምን ማለት ነው?
“የቸኮለ…..”
ቀኑ የመስከረም ዋዜማ ነው። የመንደሩ ወጣት
ወንዶች ተጠራሩና ወደወንዝ ወረዱ። ልብሳቸውን
አወላለቁ። ፎጣቸውን፣ ጃኬታቸውን፣ ካኔትራቸውን፣
የውስጥ ሱሪያቸውን፣ ቁምጣቸውን፣ ካልሲያቸውን፣
ጫማቸውን ባንድ ላይ ከመሩ። ከዚያም ወደወንዙ
እየዘለሉ ገቡ። ሲዋኙ፣ ሲዋኙ ዋሉ። ሰማዩ ዳመነ፤
ጉርምርምታ ተሰማ፤ የመብረቅ ብልጭታው ተደጋገመ። ወጣቶቹ ዋናቸውን
አቋረጠው ወደልብሳቸው እየተሯሯጡ ሄዱ። ያገኙትን ልብስ እያነሱ በችኮላ
መልበስ ጀመሩ።
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. ወጣቶቹ ተጠራርተው ወደወንዝ የወረዱት ለምንድን ነው?
ለ. ወጣቶቹ ዋናቸውን ያቋረጡት ለምንድን ነው?
ሐ. በአካባቢያችሁ በመስከረም ዋዜማ ወጣቶች ምን ያደርጋሉ? ለምን?
መ. የወጣቶቹ ስህተት ምንድን ነበር?
12 አማርኛ 2ኛ ክፍል ~ የተማሪ መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 1 አልባሳት 02
የቃላት አጠቃቀም
ለሥዕሎቹ መጠሪያ ቃላት ጻፉ።
ሀ ለ ሐ
ቅድመማዳመጥ
ለሚከተሉት ቃላት ፍቺ ጻፉ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ለ. ጓ-ደ-ኞ-ቿ መ. እ-ስ-ክ-ር-ቢ-ቶ
ቁ ጓ ተ ሸ ይ ጣ
ዝ ጫ ሰ ሚ
ቢ ኛ ደ መ ቀ ና
አቀላጥፎ ማንበብ
“ታጥቦ ጭቃ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
1.3.4 መጻፍ
ሀ. ካ-ኔ-ት-ራ-ቸ-ው-ን ሐ. ካ-ል-ሲ-ያ-ቸ-ው-ን
ለ. ቁ-ም-ጣ-ቸ-ው-ን
ሀ. ጠራ ለ. ወረደ ሐ. ዘመረ
ሀ. ጫማ ለ. ካኔትራ ሐ. ፎጣ መ. ካልሲ
1.3.5 ክለሳ
ሀ. ልብስ ለ. ፎጣ ሐ. ካልሲ መ. ጫማ
ምሳሌ፡-
ይታጠባል ይለቀማል
ይሰጣል
ልብስ ይደርቃል ጥጥ
ይተኮሳል
ይለበሳል
ቅድመማዳመጥ
ስለጉንዳን የምታውቁትን ተናገሩ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ለ. ሐ-ም-ሌ መ. መ-ስ-ከ-ረ-ም
ዙሪያክብ ጨዋታ
ናሆም፣ ዘውዲቱ፣ ዘሃራና ሀሰን የአንድ ሰፈር ልጆች ናቸው። ዛሬ እለቱ
እሁድ ነው። ከእነዘውዲቱ ሰፈር ጠባብ ሜዳ አለ። ሜዳው ላይ ክብ ሰርተው
ይጫወታሉ። የመሀል ዳኛው ናሆም ነው።
(ከአማርኛ እንደአፍ መፍቻ ቋንቋ 2ኛ ከፍል መመማሪያ መጽሐፍ መጠነኛ ለውጥ ተደርጎ የተወሰደ)
ቅድመንባብ
ሀ. ሥዕሉንና ርዕሱን አስተውላችሁ ስለታሪኩ ገምቱ።
“ሰኞ ማክሰኞ”
ይቤላ፣ ሰሚራና አረጋ ከግቢው ወለል ላይ መስመር
አዘጋጁ። መስመሮቹ ተገጣጥመው ሰባት ክፍሎችን
ሠሩ። የመጀመሪያውን የመስመር ክፍል “ሰኞ”
አሉት። በመቀጠል እያንዳንዱን የመስመር ክፍል 1 2 3 4
5 6 7
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
በሚከተሉት ሥዕሎች የልጆቹን ልብሶች መጠሪያ ቃላት ጻፉ።
5 6 7
1 2 3 4
ቅድመማዳመጥ
ስለምስጥ የምታውቁትን ተናገሩ።
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. እ-ሰ-ጥ-ሀ-ለ-ሁ ለ. ሁ-ለ-ታ-ች-ን-ም
አቀላጥፎ ማንበብ
“ዙሪያክብ ጨዋታ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
2.1.4 መጻፍ
ለ. ተ-ጫ-ወ-ች መ. እ-የ-ዘ-ለ-ለ-ች
ሀ. ክብ ለ. ሰፈረ ሐ. ጀመረ
ቅድመማዳመጥ
ሀ. ስለወቅቶች የምታውቁትን ተናገሩ?
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. ክረምት ሐ. ጥቅምት
ለ. ግንቦት መ. መጋቢት
ሀ. ይ-ዘ-ራ-ል → ይዘራል
ለ. ይ-ሰ-በ-ሰ-ባ-ል
ሐ. ይ-ጎ-መ-ራ-ል
መ. ያ-ሸ-ታ-ል
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
“በውድቅት ሌሊት”
ሌሊቱ ተጋምሶ ውድቅት ላይ ነው። ኃይለኛ ዝናብ ይዘንባል። “በዛብህ!
በዛብህ! ኧረ በዛብህ!” ተጣራች ባለቤቱ ማለፊያ። “ምን ሆንሽ?” አለ በዛብህ፤
“ምነው! አንተዬ አይታይህም እንዴ?” አለችው። “ምኑ?” በማለት ዙሪያውን
ሲመለከት፣ ቤቱ ውስጥ ጎርፉ ገብቶ ሞልቶታል። “ኧረግ! ኧረግ! እንዴት
ጉድ ተሠራን! በይ ነይ ተከተዪኝ! ‘ሠርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ’ አለ ያገሬ
ሰው” አለና፣ ዝናብ እየመታቸው የጎርፉን ማፋሰሻ ቦይ መቆፈር ጀመሩ።
ቅድመንባብ
ሀ. ሥዕሉንና ርዕሱን በማስተዋል ታሪኩ ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ።
አደይ
ክረምቱ አልፎ መስከረም ጠብቷል። ልምላሜው
ቀልብን ይሠርቃል። የንፋሱ ሽውታ መንፈስን
ያድሳል። አበባ የዛሬዋን ቀን በጣም ናፍቃታለች።
ትምህርትቤት ከተዘጋ ኹለት ወራት አልፈዋል።
ሐምሌንና ነሐሴን ቤተሰቦቿን ሰትረዳ ከርማለች።
ዛሬ የትምህርትቤት መከፈቻ ቀን ነው። አበባ
የትምህርትቤት ልብሷን ለብሳ በጧቱ ከቤቷ ወጣች። ከሩቅ ጓደኛዋን አየቻት።
ድኅረንባብ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. አበባ ቀኗን የናፈቀቻት ለምንድን ነው?
ለ. በመስከረም ወር ምን ዓይነት አበባዎች ይታያሉ?
ሐ. አበባ ቤተሰቦቿን ምን ዓይነት ሥራ ትረዳቸዋለች?
22 አማርኛ 2ኛ ክፍል ~ የተማሪ መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 2 ወቅቶች !2
የቃላት አጠቃቀም
በ“ሀ” ሥር ለቀረቡት ቃላት ተቃራኒ ከ“ለ” ሥር መርጣችሁ አዛምዱ።
“ሀ” “ለ”
1. ቅርብ ሀ. መለያየት
2. ክረምት ለ. መሸ
3. ዝግ ሐ. ክፍት
4. ጠባ መ. በጋ
5. መገናኘት ሠ. ሩቅ
ረ. መጥፋት
ቅድመማዳመጥ
የሚከተሉትን ቃላት ፍቺ ተናገሩ።
ሀ. ወቅት ለ. ጸደይ ሐ. በልግ መ. በጋ ሠ. ክረምት
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. ገ-በ-ሬ-ዎ-ች ሐ. ወ-ቅ-ቶ-ች
ለ. ሰ-ብ-ሎ-ች መ. ም-ን-ጮ-ች
አቀላጥፎ ማንበብ
“በውድቅት ሌሊት” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
2.2.4 መጻፍ
ሀ. መስከረም ሐ. ጠየቀ
ለ. ፈነዳ መ. ልምላሜ
ቅድመማዳመጥ
ሥዕሉን አስተውላችሁ ስለታሪኩ ገምቱ።
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ምሳሌ፡- የአክስት ልጅ
ክረምትና በጋ
የካቲት መውቂያ ነው/ ክምሩ ፈረሰ፣
ቅድመንባብ
ሥዕሉንና ርዕሱን አስተውሉና ታሪኩ ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ።
ወይ አለማስተዋል!
አንድ መንገደኛ ከገበያ ወደቤቱ ሲመለስ
ደከመውና ከሾላ ዛፍ ሥር ጋደም አለ።
ዙሪያውን በዓይኑ መቃኘት ጀመረ።
ባጋጣሚ ወደላይ ሲያንጋጥጥ የሾላ ፍሬ
አየ። ወደታች ሲያማትር ደግሞ በዱባው
ሐረግ ላይ ትልቅ የዱባ ፍሬ አየ። እጅግ
ተደነቀና ተፈጥሮን ወቀሰ።
ድኅረንባብ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
ቅድመማዳመጥ
የሚከተሉትን ቃላት ፍቺ ተናገሩ።
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
2.3.4 መጻፍ
3. አጣምራችሁ ጻፉ።
2.3.5 ክለሳ
ምሳሌ፡- ወቃ - እየተወቃ
ቅድመማዳመጥ
ርዕሱን አስተውሉና ታሪኩ ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ።
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ለ. አባ ሲሏቸው ቆብ የላቸው።
“ብልጡ ቀበሮ”
አንድ ቀን አንዲት ድመት ከአንድ ነጋዴ ዓይብ ሠርቃ ትሄዳለች። በዚህ
ጊዜ አንድ ውሻ ያያታል። አይቡን ሊወስድባት ፈለገና ተጠጋት። ድመቷ
ግን የውሻውን ዓይን መቧጨር ጀመረች። ውሻው ደግሞ ይነክሳት ጀመር።
ድመቷ አላዋጣ ሲላት “ቀበሮ ይዳኘን” አለችው። ውሻውም ተስማማ። ቀበሮም
ጉዳያቸውን ካዳመጠ በኋላ “የማትረቡ ናችሁ!” አለና ዓይቡን ከኹለት እኩል
አካፈላቸው። ውሻው ግን “የእኔ ድርሻ አንሷል!” ብሎ ተቃወመ። ቀበሮም
“አዎ!... እውነትም” አለና ከድመቷ አንድ ጉርሻ ጎረሰለት። ድመቷም በተራዋ
እንዴ! የእኔ ድርሻ ቀንሷል! አለች። ቀበሮም “ልክ ነው፤ አንሷል”፤ አለና
ከውሻው ድርሻ ጎረሰለት። እንዲህ እያለ በየተራ የሁለቱንም ድርሻ እየጎረሰ
ባዷቸውን አስቀራቸው።
ቅድመንባብ
ሀ. ሥዕሉን አስተውሉና ስለታሪኩ ገምቱ።
መንገደኛውና ተኩላ
አንድ መንገደኛ ከዛፍ ግንድ ጋር የታሰረ ተኩላ
ያገኛል። ተኩላውም “እባክህ ፍታኝ” አለው።
መንገደኛውም “ምንገዶኝ” ብሎ ፈታው። በመቀጠል
ተኩላ “እበላሀለሁ” አለው። “በል ጦጢት ትፍረድና
ትበላኛለህ” አለው። ሁለቱም ተያይዘው ወደጦጢት
ድኅረንባብ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
በምሳሌው መሠረት ዓረፍተነገሮቹን አሟልታችሁ ጻፉ።
ቅድመማዳመጥ
ሀ. የእንቆቅልሽን የአጨዋወት ቅደምተከተል ተናገሩ።
ቃላት
አቀላጥፎ ማንበብ
“ብልጡ ቀበሮ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
3.1.4 መጻፍ
ጦጢት ምን አደረገች?
3.1.5 ክለሳ
ሀ. ዳኛ ሆነች ጦጢት
መልስ ምድብ
ተቀማጭ፡- ድንጋይ ሕይወት አልባ
ተንቀጥቃጭ፡- ቄጤማ ከአትክልት
ሀ. ሳታጠባ የምታሳድግ
ቅድመማዳመጥ
ሥዕሉን ተመልከቱና ስለታሪኩ ገምቱ።
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች ባደመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. ኩ-ር-ም-ት ለ. መ-ን-ደ-ር
ሐ. ደ-ፈ-ረ-ሰ መ. ወ-ረ-ወ-ረ-ለ-ት
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
ቀበሮና ቁራ
አንዲት ቀበሮ ምግብ ፍለጋ ብዙ ተንከራተተች። በጣም ሰለደከማት ከዛፍ
ሥር ተቀመጠች። ቁራ፣ ሙዳ ሥጋ ባፉ ይዞ ከዛፍ ላይ አረፈ። ቀበሮ ድንገት
አየችው። ሆዷ በረሀብ ተላወሰ። ዘዴ ዘየደች። ድምጽዋን አለሰለሰችና “አንተ
ቁራ እንደመልክህ ድምጽህ ካማረ ንጉሥ ትሆናለህ!” አለችው። ቁራው
በሰማው ነገር በጣም ተደሰተ። ድምጹን ለማሰማት አፉን ሲከፍት ሙዳ
ሥጋው ወደቀ።
ቅድመንባብ
ሀ. ሥዕሉንና ርዕሱን በትክክል በማስተዋል ስለታሪኩ ገምቱ።
“ብልኋ ሴት”
በባለቤቷ ባህርይ የተቸገረች አንዲት ሴት ነበረች። አንድ
ቀን የሴት አያቷን ምክር ጠየቀች። አያቷም የአንበሳ
ጎፈር እንድታመጣ መከሯት። አንበሳውን እንዴት
እንደምትቀርብ ስታወጣ ስታወርድ ሰነበተች። ከዚያም
ብዙ ሥጋ ይዛ ወደጫካ ሄደች። በመጀመሪያው ቀን
እጅግ ብዙ ሜትሮችን ርቃ ጉማጅ ሥጋ ወረወረችለት።
በሚቀጥለው ቀን ቀረብ ብላ ሥጋውን አስቀመጠች። በዚህ ዓይነት ሁኔታ
ርቀቷን እየቀነሰች ወደአንበሳው ተጠጋች። አንበሳውም ጠረኗንና ዳናዋን
እየለመደ መጣ። በመጨረሻም ይታከካት ጀመር።
ድኅረንባብ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. ስለታሪኩ ቀድማችሁ የገመታችሁት ትክክል ነበር? ለምን?
ለ. አያቷ የአንበሳ ጎፈር እንድታመጣ ያዘዟት ለምን ይመስላችኋል?
ሐ. አንበሳ ምን ዓይነት እንስሳ ይመስላችኋል? እንዴት አወቃችሁ?
መ. ሰዎች ከዱር እንስሳት ጋር መላመድ ይችላሉ? እንዴት?
ቅድመማዳመጥ
ለሚከተሉት ቃላት ፍቺ ስጡ።
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች ባደመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
3.2.4 መጻፍ
ሀ. ፈረስ ለ. ዶሮ ሐ. ጃርት መ. በሬ
3.2.5 ክለሳ
ሀ. ቅርጫ ሥጋ ለ. ሙዳ ሥጋ ሐ. ብልኋ ሴት
ቅድመማዳመጥ
ሀ. መካን፤ ማለት ምን ማለት ነው?
ቃላት
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
የተዛባ ፍርድ
አንድ ቀን አንበሳ፣ ነብር፣ ጅብና አህያ ክፉ ቀን መጣባቸው። ተሰበሰቡ።
“የሠራነው ኃጢያት ነው” ለዚህ ያበቃን በማለት ኃጢያታቸውን ለመናዘዝ
ተስማሙ። የከፋ ኃጢያት የሠራውም ሊፈረድበት ውል ገቡ። በመጀመሪያ
አንበሳ ተነሳና “አንዲት ላም ከበረት ስትወጣ አግኝቼ በላኋት” አለ። እንስሳቱም
“ከበረት ማን ውጪ አላት? አንተ ጥፋተኛ አይደለህም!” አሉት። ቀጥሎ
ነብር፣ ተነሳና “በጫካ ውስጥ ፍየል አግኝቼ በልቻለሁ።” አለ። እነሱም
“ከእረኞች ማን አምልጪ አላት? አንተ ጥፋተኛ አይደለህም” አሉት።
ቅድመንባብ
ለሚከተሉት ቃላት ፍቺ ስጡ።
የፍኖተሰላም ስያሜ
ጣሊያኖች ኢትዮጵያን በቅኝግዛት ለመያዝ አስበው በ1928 ዓ.ም ወረራ
አካሄዱ። የኢትዮጵያ አርበኞችም በዱር በገደሉ ተፋለሙ። ከዐምስት ዓመታት
በኋላ አርበኞች ጣሊያኖችን አሸነፉ። ጣሊያኖችም እግሬ አውጪኝ፤ ብለው
ወደሀገራቸው ተመለሱ። አፄ ኃይለሥላሤ በጦርነቱ ወቅት ወደውጪ
ሀገር ሄደው የዓለም መንግሥታት ወረራውን እንዲያወግዙ ሲጠይቁ ቆዩ።
ጣሊያኖች ተሸንፈው ሲወጡ አፄ ኃይለሥላሤ በሱዳን በኩል ወደሀገራቸው
ተመለሱ። ወደአዲስ አበባ ለመጓዝ “ወጀት” ከምትባል ከተማ አደሩ።
በማግስቱ ወደአዲስ አበባ ለመጓዝ ሲነሱ “በሰላም ወደሀገራችን ስለገባንና
የሰላም መንገድ ስለሆነልን “ወጀት” የምትባለውን ከተማ “ፍኖተሰላም” ትባል
ብለው ሰየሟት።
ድኅረንባብ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
በምሳሌው መሠረት ጻፉ።
ቅድመማዳመጥ
ሀ. በቅሎዎች የሚራቡት እንዴት ነው?
ድኅረማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎች ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. እ-ም-ቢ-ታ-ዋ-ን ሐ. የ-ተ-ራ-ራ-ቁ-ት-ም
ለ. እ-ን-ስ-ሳ-ዋ
ምሳሌ፡- ነጨ → ነጭቻለሁ
ሀ. አመለጠ ለ. በላ ሐ. አገኘ መ. ነጨ
አቀላጥፎ ማንበብ
“የተዛባ ፍርድ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
3.3.4 መጻፍ
ሀ. ኢ-ት-ዮ-ጵ-ያ
ለ. መ-ን-ግ-ስ-ታ-ት
ሐ. አ-ር-በ-ኞ-ች
መ. ሰ-የ-ሟ-ት
ለ. ባሕር - ዳር
3.3.5 ክለሳ
ምሳሌ፡- ሀ. ባሕርዛፍ
ለ. ደብረኤልያስ
ቅድመማዳመጥ
ከዚህ በፊት የምታውቋቸውን የፍራፍሬ ዓይነቶች ተናገሩ።
ድኅረማዳመጥ
ሙዝን እንዴት መመገብ እንደሚቻል
በዝርዝር ጻፉ።
ቃላት
ሀ. ፍ-ራ-ፍ-ሬ ሐ. የ-ሚ-ራ-ባ
ለ. ተ-ገ-ን-ፍ-ቶ መ. ተ-ፈ-ጭ-ቶ
ምሳሌ፡- ፍራ - ፍሬ → ፍራፍሬ
እኔ ማን ነኝ?
ከፍራፍሬዎች እመደባለሁ። ቅርፄ ክብ ነው። ስበስል መልኬ ወደቢጫ
ያደላል። ተልጬ እበላለሁ። በውስጤ ከስምንት እስከ አሥር የሚደርሱ
ክፍልፋዮች አሉኝ። በየክፍልፋዮቹ ውስጥ ኹለት ወይም ከዚያ በላይ ዘሮች
አሉኝ። ሰዎች ሲመገቡኝ በጣም እጣፍጣለሁ። በውስጤ የያዘኩትም ዘር
በቅሎ ራሴን ይተካል። እኔ ማን ነኝ?
ቅድመንባብ
ሥዕሎቹን በማስተዋል ታሪኩ ስለምን እንደሚገልፅ ገምቱ።
“ሁለቱ ጓደኛሞች”
ሰላጣና ቆስጣ በጣም የሚዋደዱ አብሮ አደጎች ነበሩ።
ቆስጣ ለሰላጣ ከፍተኛ አክብሮት አለው። ሰላጣም
ቆስጣን እጅግ ይወደዋል። ሁለቱም በአፈር ውስጥ
ያሉ ማዕድናትን ይመገባሉ። ፀሐይን ይሞቃሉ፣
ዉኃም እኩል ይጠጣሉ። አንድ ቀን ሰዎች ቆስጣን ቀንጥሰው ወሰዱ።
ቆስጣም በጣም ተኩራራና በንቀት አየው።
“ሰዎች በየቀኑ እየቀነጠሱ ይወስዱኛል። አንተን ግን መጠቀም አልፈለጉም።
ለምን ይመስልሃል?” በማለት ሰላጣን ጠየቀው። ሰላጣም “አይ ጓደኛዬ!
አንተ መልክህ ጠቆር ቢልም ይፈልጉሀል። ስለዚህ ትበላለህ፤ እኔ ግን
መልኬ ፈካ ያለ ቢሆንም ለማባያነት ሎሚ/አቼቶ፣ ቃሪያ፣ ቲማቲም
ስለምፈልግ ወጪዬ ብዙ ነው” በማለት መለሰለት።
የቃላት አጠቃቀም
ቆስጣንና ሰላጣን በማወዳደርና በማነጻጸር ጻፉ።
ቅድመማዳመጥ
ሙዝ “ሁለገቡ ፍራፍሬ” የተባለው ለምን ይመስላችኋል?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
አቀላጥፎ ማንበብ
“እኔ ማን ነኝ?” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
4.1.4 መጻፍ
ምሳሌ፡-
ሀ. ቆስጣ ለ. ዛፍ ሐ. ጥጥ መ. አበባ
ሙዝ ብርቱካን
ይበላሉ።
ልጣጩ ፊትን ብዙ ክፍሎች
ያስውባል። አሉት።
ቅድመማዳመጥ
ሀ. ሰዎች ደስተኛና ጤነኛ የሚሆኑት እንዴት ነው?
ድኅረማዳመጥ
የሥዕሎቹን መጠሪያ ቃላት ተናገሩ።
ሀ ለ ሐ መ
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
“ወይ አለማወቅ!”
“ተረኛ! ተረኛ!” አለ ነርሱ። ወይዘሮ ታሪኳ “አቤት!” ብለው የኹለት
ዓመት ልጃቸውን ይዘው ገቡ። “ምኑን ነው ያመመው?” ዶክተሯ ጠየቁ።
“አያዩትም! ጠጉሩ ሳስቷል፣ ሆዱ ተነፍቷል፤ ድዱም ይደማል” አሉ
ወይዘሮ ታሪኳ ልጃቸውን በአዘኔታ እየተመለከቱ።
ቅድመንባብ
ሥዕሉን በመመልከት የተረዳችሁትን ግለጹ።
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. በግቢያችሁ/በጓሯችሁ ምን ዓይነት አትክልትና ፍራፍሬ በቅለዋል?
ለ. በጠባብ ቦታ በምን ዓይነት ዕቃዎች አትክልትን ማምረት ይቻላል?
ሀ. የታሪኩን ሐሳብ አጠር አድርጋችሁ ለክፍል ጓደኞቻችሁ ንገሯቸው።
ለ. የታሪኩን ሐሳብ በአንድ ዓረፍተነገር ግለጹ።
የቃላት አጠቃቀም
በምሳሌው መሠረት ሌሎች ቃላት ጻፉ።
ፍራፍሬ → ብርቱካን
ቅድመማዳመጥ
ፈጣን ሯጭ ለመሆን ምን ያስፈልጋል፤ ብላችሁ ታስባላችሁ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. ባለታሪኳ ማን ናት?
ቃላት
ሀ. የ-ተ-ወ-ለ-ድ-ኩ-ት ሐ. የ-ም-መ-ገ-በ-ው
ለ. የ-ም-ት-ነ-ግ-ረ-ን መ. የ-ም-ሠ-ራ-ው
ዱባ ሥጋ ሽሮ ክክ ድንች ምሥር
አቀላጥፎ ማንበብ
“ወይ አለማወቅ!” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
4.2.4 መጻፍ
1. ቃላቱን ድምፅ በማሰማት አንብቡና ጻፉ።
4.2.5 ክለሳ
ሀ. ጠጉሩ ለ. ሰውነቱ ሐ. ድዱ መ. ሆዱ
ቅድመማዳመጥ
ለሚከተሉት ቃላት ፍቺ ጻፉ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ለ. መ-ም-ረ-ጥ መ. መ-ቆ-ፈ-ር
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
የሐና አመጋገብ
ሐና የኹለተኛ ክፍል ተማሪ ናት። አንድ ቀን የሳይንስ መምህራቸው
“ሁሉንም የምግብ ዓይነቶች በተመጣጠነ መልኩ መመገብ ያስፈልጋል፤
የተመጣጠኑ ምግቦች ለሰውነታችን ጥንካሬ ይሰጣሉ፤ የአስተሳሰብ እድገት
ያመጣሉ። አልፎ ተርፎም ውበትን ይጠብቃሉ። በተለይ አትክልትና
ፍራፍሬን መመገብ ጤናማ እንድንሆን ትልቅ አስተዋፅኦ አላቸው” በማለት
53 አማርኛ 2ኛ ክፍል ~ የተማሪ መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 4 የጓሮ አትክልት $3
አስተማሯቸው። ሐናም ከትምህርትቤት ስትመለስ ለቤተሰቦቿ “ከዛሬ ጀምሮ
ይሄን ምግብ አልወድም፤ ያንን እወዳለሁ ብዬ አልመርጥም፤ እናንተንም
አላስቸግርም አለቻቸው።”
ቅድመንባብ
ሥዕሉን ተመልክታችሁ ታሪኩ ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ።
ዝንጀሮና የአፕል ፍሬ
በወንዝ አጠገብ የበቀለች አፕል በአካባቢዋ ላሉ
እንስሳት ሲሳይ ነች። ዝንጅሮም የአፕል ፍሬ
እየተመገበች እምቡጥ ፅጌረዳ መስላ ትኖራለች።
አንድ ቀን ዝንጀሮ ለመዝናናት አፕሏን ይዛ
ወደወንዝ ወረደች። በወንዙ ዳር ዐዞ አገኘች።
ስለደነገጠች ቶሎ ብላ አፕሏን በዐዞው አፍ
ውስጥ ከተተችው። ዐዞውም እያጣጠመ ተመገበ።
ለእርሷም እንዲያመጣላት ሚስቱ ጠየቀችው።
ዝንጀሮን አመሰግኖ ወደቤቱ ሄደ። ለባለቤቱም ስለውሎው ነገራት።
በማግስቱ ዝንጀሮዋ ብዙ አፕል ይዛ መጣች። ዐዞውም ዝንጀሮዋን ወደቤቴ
ልውሰድሽ ብሎ በጀርባው አዝሎ ወደቤቱ ጉዞ ጀመሩ። ከወንዙ መሀል
ሲደርሱ “ባለቤቴ ልብሽን ትፈልገዋለች” አላት። ዝንጀሮም “ውይ! ከአፕሉ
ዛፍ ላይ ትቼው ነው የመጣሁት፤ መልሰኝና አውርጄ ልስጥህ” አለችው።
ዐዞም ልቧን ለመቀበል ጓጉቶ ወደወንዙ ዳር መለሳት።
የቃላት አጠቃቀም
በምሳሌው መሠረት ሌሎች ሐረጋት ጻፉ።
ምሳሌ፡- የአፕል ፍሬ
ቅድመማዳመጥ
ከርዕሱ ምን ተረዳችሁ?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. ቦታ ለ. ስፍራ ሐ. ማጤን መ. ፍል
አቀላጥፎ ማንበብ
“የሐና አመጋገብ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
4.3.4 መጻፍ
ሀ. አ-መ-ሰ-ገ-ነ ሐ. የ-አ-ፕ-ል-ፍ-ሬ
ለ. ከ-ተ-ተ-ች-ው መ. በ-ማ-ግ-ስ-ቱ
ምሳሌ፡-
ዝንጀሮ የአፕል ዛፍ
ቅድመማዳመጥ
የአካባቢያችሁን ንፅህና ለመጠበቅ ቤተሰቦቻችሁ ምን ያደርጋሉ?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. ማጠራቀሚያ ለ. መትፋት
ሀ. ሳሙና ሐ. ማቃጠል
ለ. ጉድጓድ መ. መሸፈን
“በቁማችን ሞተናል!”
አቶ አግማሴ “እትትት….. ውይ! ወይኔ! ራሴ!” እያሉ ይጮሃሉ።
ጎረቤታቸው አቶ አያሌው፣ “ምን ሆነሃል? ያችወባ ተነሳችብህ እንዴ?
ይገርማል! በገዛ እጃችን የበሽታ ጎሬ እንሁን!” አሉ አቶ አግማሴ ጥርሳቸውን
እያፋጩ፣ “እስቲ ተመልከት! በዙሪያችን ያለው ዉኃ አረንጓዴ ሠርቶ!
የቆሻሻው ሽታስ አፍንጫችንን በጥሶ ሊጥለው አይደል!?” አሉ። አቶ
አያሌውም “እኛማ በቁማችን ሞተናል እኮ! ነገ ማህበረሰቡን ሰብስቤ
የፅዳት ዘመቻ አውጃለሁ” አሉና እጃቸውን አወናጨፉ።
ቅድመንባብ
ርዕሱን በማንበብ ታሪኩ ስለምን እንደሚገልፅ ገምቱ።
በሽታን መከላከል
በንፅህና ጉድለት የሚመጡ በሽታዎችን መከላከል ያስፈልጋል። ለምሳሌ
ጠጉርን፣ ገላንና እጅን በመታጠብ፣ ልብስን በማጠብ የተስቦ በሽታን
እንከላከላለን። ቆሻሻን ሰብስቦ በማቃጠልና በመፀዳጃቤት በመጠቀም
የተቅማጥ፣ የዓይንማዝና የጉንፋን በሽታዎችን መከላከል ይቻላል።
በክረምት የሚያቁሩ ኩሬዎችን በማፋሰስና በማድረቅ የወባ ትንኝ እንዳትራባ
በማድረግ የወባ በሽታን መቀነስ ይቻላል።
የቃላት አጠቃቀም
የአካባቢ ንፅህናን ለመጠበቅ ስለሚያስችሉ አራት ተግባራት ጻፉ።
ምሳሌ፡- ቆሻሻን ሰብስቦ ማቃጠል።
ቅድመማዳመጥ
ለቃላቱ/ሐረግ ፍቺ ስጡ።
ሀ. መፀዳጃቤት ለ. ኮረና ሐ. ተላላፊ በሽታዎች
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. የታሪኩን ሐሳብ በቃል ለክፍል ጓደኞቻችሁ ተናገሩ።
ለ. የተከናወኑ ድርጊቶችን በቅደምተከተል ግለጹ።
ቃላት
መፀዳጃ
ቤት
5.1.4 መጻፍ
ሀ. መ-ከ-ላ-ከ-ል
ለ. የ-ዓ-ይ-ን-ማ-ዝ
ሐ. የ-ወ-ባ- በ-ሽ-ታ
መ. ተ-ቅ-ማ-ጥ
ቅድመማዳመጥ
ስለቆሻሻ መጣል በአካባቢያችሁ ምን ምን ታዘባችሁ?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሐ. ከታሪኩ ምን ተረዳችሁ?
ቃላት
“ታሞ ከመማቀቅ…”
ድመትና ውሻ በአንድ ቤት ውስጥ ተረዳድተው ይኖራሉ። አካባቢያቸውን
በማፅዳት ግን ፍጹም አይግባቡም።
ድመት፣ እባክህ የአካባቢያችን ንፅህና በመጓደሉ ዝንቦችና ጉንዳኖች/
ዘመሚቶች አላስቀምጥ አሉን፤ አለችው።
ውሻ፣ ይህ የሆነው በአንቺ ምክንያት ስለሆነ ራስሽን ጠይቂ።
ድመት፣ ምነው… እኔማ ጽዳትን በመጠበቅ በኩል እታወቃለሁ፤
ዓይነምድሬንም ሆነ ሽንቴን ጉድጓድ ቆፍሬ እቀብራለሁ።
ውሻ፣ እኔም የምችለውን ሠርቻለሁ።
ድመት፣ አንተ እኮ! ዓይነምድርህንም ሆነ ሽንትህን በአገኘህበት ቦታ
ትፅዳዳለህ። ‘ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ’ እንደሚባለው
ጥንቃቄ ያስፈልጋል፤ አለችው።
ውሻ፣ እውነት ብለሻል ትኩረት ባለመስጠቴ አካባቢውን በክዬዋለሁ፤
ለወደፊቱ አስተካክላለሁ፤ አለ።
ቅድመንባብ
ርዕሱን በማንበብ ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ።
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
አካባቢን የሚበክሉ ነገሮችን ዘርዝራችሁ ጻፉ።
ቅድመማዳመጥ
ሥዕሉን በመመልከት የተረዳችሁትን ተናገሩ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
አቀላጥፎ ማንበብ
“ታሞ ከመማቀቅ...” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
5.2.4 መጻፍ
ሀ. ሥራ ለ. ወራት ሐ. መተባበር
ዓለሙ፡- “___________?”
ዓለሙ፡- ___________
ቅድመማዳመጥ
ሥዕሉን አስተውላችሁ ስለታሪኩ ገምቱ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል
መልሱ።
ቃላት
ሀ. አ-ስ-ጠ-ራ-ቸ-ው ሐ. የ-ሚ-በ-ሰ-ብ-ሱ
ለ. እ-ቀ-ብ-ራ-ለ-ሁ መ. እ-ለ-ያ-ቸ-ዋ-ለ-ሁ
ጣናን እንከባከብ
የጣና ሐይቅ ከባሕር ዳር ከተማ በስተሰሜን አቅጣጫ ይገኛል። ሐይቁ
በየጊዜው ለተለያዩ ችግሮች የተጋለጠ ነው። ከችግሮቹ መካከል አንደኛው
በሐይቁ አካባቢ ያሉ ኗሪዎች ልብሳቸውን ያጥቡበታል፤ ሰውነታቸውን
ይታጠቡበታል። ሌሎች ቁሳቁሶችንና ተሽከርካሪዎችን ያፀዱበታል።
ቅድመንባብ
ከርዕሱ ምን ተረዳችሁ?
“ሁሉም ቢተጋገዝ”
ጊዜው ክረምት ነው። ከላይ ዶፍ ዝናብ ይዘንባል። ጎርፉ ከየቤቱ የሚወጣውን
ቆሻሻ በዉኃ ማፋሰሻ ቦይ ይጨምራል። ኗሪዎችም ዝናቡን ተገን አድርገው
በማዳበሪያ ያጠራቀሙትን ቆሻሻ በየቱቦው ይጥላሉ። ዝናቡ ማባራት ጀመረ።
የቃላት አጠቃቀም
ለቃላቱ ተመሳሳይ ፍቺ ጻፉ።
ቅድመማዳመጥ
ለቃላቱ ተመሳሳይ ጻፉ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. አርሶአደሩ ልጆቹን ያስጠራቸው ለምንድን ነው?
ለ. የአርሶአደሩን ምክር ለክፍል ጓደኞቻችሁ ተናገሩ።
ሐ. እናንተስ ወላጆቻችሁ ምን ዓይነት ምክር ይመክሯችኋል?
ቃላት
ለቃላቱ ተመሳሳይ ፍቺ ጻፉ።
5.3.4 መጻፍ
ሀ. ዶፍ ለ. ተገን ሐ. አባራ
ምሳሌ፡-
ቆሻሻ
ወረቀት ፌስታል
መንስኤ ውጤት
ሰዎች በመሳሳታቸው
ቅድመማዳመጥ
ሀ. በአካባቢያችሁ ምን ዓይነት በዓላትን ታከብራላችሁ?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. አርሶአደሮች
ለ. ቃላዊ ሀብቶች
ሐ. ባህላዊ ዘፈኖች
ምሳሌ፡- የሠርግ
የሠርግ ዘፈኖች
የሠርግ ቤት ከዋዜው ጀምሮ በሠርግ ዘፈኖችና በእልልታ ይደምቃል።
በሙሽራዋ ቤት ከሚዘፈኑ ዘፈኖች መካከል ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው።
አሳድገዋታል እያቆላመጡ።
አበራች እንደፀሀይ።
ወሰደሽ አስተማሪ።
ቅድመንባብ
ርዕሱን አንብቡና የተረዳችሁትን በቃል ግለጹ።
እረኛውና ዋሽንቱ
አንድ ቀን እረኛው በጧት ተነሳ:: ዋሽንቱን ያዘና ወደግጦሽ ቦታ ወረደ።
ከብቶቹን አሰማራ። ከዚያም ዋሽንቱን እየነፋ፡-
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
በምሳሌው መሠረት ሌሎችን አገላለጾች አሟልታችሁ ጻፉ።
ሀ. ክራር ሐ. አታሞ
ለ. ማሲንቆ መ. ደወል
ቅድመማዳመጥ
የሚከተሉትን ጥያቄዎችን በቃል መልሱ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
አቀላጥፎ ማንበብ
“የሠርግ ዘፈኖች“ የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
6.1.4 መጻፍ
6.1.5 ክለሳ
ራሔል፡- ____________
ሀና፡- ____________
“ሀ” “ለ”
1. አቆላመጠ ሀ. ጥንታዊ
2. ወሰደ ለ. ውበቷ ጠፋ
3. ዘፈነ ሐ. አዋረደ
4. ዘመናዊ መ. መለሰ
ሠ. አለቀሰ
ቅድመማዳመጥ
ሀ. ሥዕሉን አስተውሉና ስለታሪኩ ገምቱ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ምሳሌ፡- ማሲንቆ
“የከበሮ አዘገጃጀት”
ከበሮ ከምት የሙዚቃ መሣሪያዎች መካከል አንዱ
ነው። ከበሮን ለማዘጋጀት የከብቱ ቆዳ በዉኃ ይነከራል፤
በመቀጠል በችካል ይወጠራል፤ ከጠጉሩ ጀርባ ያለው አካል
ይፋቃል፤ ከዚያም ይለፋል። ለቆዳ መወጠሪያ የሚሆነው
ወፍራም የዋንዛ እንጨት ይጠረባል። ውስጡ ደግሞ
ይቦረቦርና ክፍት ይሆናል። እንጨቱ ሞላላ ቅርፅ ሆኖ ታቹ ጠባብ፣ ላዩ
ሰፊ ክብ ቅርጽ ይኖረዋል። ተለፍቶ የተዘጋጀው ቆዳ በተጠረበው እንጨት
ከላይና ከታች ባለው ቀዳዳ ላይ ተደርጎ በጠፍር እየተጠላለፈ ይወጠራል።
ከበሮው ጥሩ ድምጽ እንዲኖረው የእምቧይ ፍሬ በየጊዜው እየተቀባ ፀሐይ
ይሞቃል።
ቅድመንባብ
በበዓል ወቅት በአካባቢያችሁ ምን ዓይነት ባህላዊ ዘፈኖች ይዘፈናሉ?
ሆያ ሆዬ
የቡሄ በዓል በሚከበርበት ዕለት የሚዜም ባህላዊ ዜማ ነው። ልጆች የበዓሉ
ዕለት ከየሰፈሩ ተጠራርተው በመገናኘት በአንድ ላይ እያሸበሸቡ፡-
ሆያ ሆዬ፣ ሆያ ሆዬ፣
የእኔማ ጌታ የሰጡኝ ሙክት፣
ከግንባሩ ላይ አለው ምልክት።
ሆያ ሆዬ የኔማ ጉዴ
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
በቃላቱ ዓረፍተነገር መሥርቱ።
ቅድመማዳመጥ
ሀ. ማሲንቆና ፈረስ እንዴት ጓደኛ ሊሆኑ እንደሚችሉ ግለጹ?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
“ሀ” “ለ”
1. ተበሳጨች ሀ. አወያየች
2. ትቆረጫለሽ ለ. ተናደደች
3. አማከረች ሐ. የተፈተለ
4. ይነካኩናል መ. ትበጠሻለሽ
5. የተገመደ ሠ. ይዳስሱናል
ረ. ትስተካከያለሽ
6.2.4 መጻፍ
“ሆያ ሆዬ፣ ሆያ ሆዬ
ሆያ ሆዬ፣ የኔማ ጉዴ
ጨዋታ ነው ልማዴ።”
ሀ. በገና ዕለት
ለ. በኢድአልፈጥር ዕለት
6.2.5 ክለሳ
“ሀ” “ለ”
1. ጀርባ ሀ. ዝግ
2. ላይ ለ. ፊት
3. መወጠር ሐ. ታች
4. ክፍት መ. መፍታት
5. ማሰር ሠ. ማላላት
ረ. መቀጠል
ቅድመማዳመጥ
ሀ. ባካባቢያችሁ የሚከናወኑትን ባህላዊ ውዝዋዜዎች ግለጹ?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
ቀረርቶና ፉከራ
ቀረርቶና ፉከራ የህብረተሰቡ ቃላዊ ሀብቶች ናቸው። ሰዎች ስሜታቸውን
በዜማና በውዝዋዜ ይገልፃሉ። በመጀመሪያ አቅራሪዎች በአንድ ጆሯቸው
ላይ ጣታቸውን ይሰኩና ከወዲያ ወዲህ እየተንጎራደዱ ያቅራራሉ።
ለምሳሌ፡- አባት የሞተ ዕለት ባገር ይለቀሳል፣
እናት የሞተች ዕለት ባገር ይለቀሳል፣
ሀገር የሞተችለት ወዴት ይደረሳል።
ሀገሬ ኢትዮጵያ ሞኝ ነሽ ተላላ ፣
የሞተልሽ ቀርቶ የበደለሽ በላ።
ጎበዝ ወይዛዝርቱ ኢትዮጵያን ጠብቁ፣
ሁሉም በሀገር ነው አልማዝና ወርቁ።
ምኒልክ ተነስቶ ባያነሳ ጋሻ፣
ግብሩ እንቁላል ነበር ይሄን ጊዜ ሀበሻ።
ማረሻው ምንሽር መጎልጎያው ጓንዴ፣
ያማራዎች መኩሪያ ወልቃይት ጠገዴ።
ቅድመንባብ
የሥዕሎቹን መጠሪያ ቃላት ተናገሩ።
የቃላት አጠቃቀም
የሐሳብ ማደራጃ ቢጋሩን በደብተራችሁ አዘጋጅታችሁ አሟልታችሁ ጻፉ።
ክራር
የክር
ባህላዊ
የሙዚቃ
መሣሪያዎች
ቅድመማዳመጥ
ለቃላቱ ተመሳሳይ ፍቺ ስጡ።
ቃላት
ሀ. ወ-ገ-ባ-ቸ-ው-ን ሐ. ማ-ን-ቀ-ሳ-ቀ-ስ
ለ. ው-ዝ-ዋ-ዜ-ዎ-ች መ. ት-ክ-ሻ-ቸ-ው-ን
አቀላጥፎ ማንበብ
“ቀረርቶና ፉከራ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
6.3.4 መጻፍ
ቅድመማዳመጥ
ሀ. ልጆች “ጥሩ ሥነምግባር አላቸው” ተብሎ የሚታሰበው ምን ምን
ሲያደርጉ ነው?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ሐ. ከታሪኩ ምን ተማራችሁ?
ቃላት
ሀ. ዓይነሥውር ሐ. ታናናሾቿ
ለ. ሥነምግባር መ. ታላላቆቿ
“ይቅርታ ጠይቂ!”
“አባዬ! አባዬ! ኧረ አባዬ!” ኤልሃና ተጣራች። “ምን ሆነሽ ነው? ኤልሃና
በጧቱ የምትጣሪው” አሏት አባቷ። ቢጃማቸውን እየቀየሩ ከመኝታቤታቸው
ሆነው ተጣሩ። “እየውልህ አባዬ ኤልሳ የእኔን ጫማዎች እያደረገችብኝ”
ብላ አለቀሰች። አባቷ ሮጠው ከልጆቻቸው መኝታቤት ገቡ። ሁለቱም
እህትማማቾች ጫማዎችን ይዘው ይታገላሉ። ወዲያው አባታቸውን እንዳዩ
ኤልሳ ጫማዎቹን ለቀቀቻቸው። ኤልሃናም ጫማዎቿን ለአባቷ እያሳየች
እንባዋን ጠራረገች። አባታቸውም “ኤልሳ በይ አሁን እህትሽን ይቅርታ
ጠይቂ! የአንቺ ያልሆነን ነገር ካልተፈቀደልሽ በስተቀር አትንኪ!” አሏት።
ኤልሳም ዝቅ ብላ እህቷን ይቅርታ ጠየቀች። ኤልሃናም “ይቅር ብዬሻለሁ”
አለቻትና ተቃቅፈው ተሳሳሙ።
ቅድመንባብ
ርዕሱን አንቡበና ታሪኩ ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ።
መስጠትና መቀበል
ኤደን፣ ናትናኤልና ዘቢባ የኹለተኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው። አንድ
ቀን ለእረፍት እንደወጡ ዘቢባ “ዶሮ እንቁላል ይጥላል” ብላ ጠየቀቻቸው
ናትናኤልም፣ “አሁን ይሄ ጥያቄ ነው?” ብሎ ሳቀባት። ኤደንም፣ “አንተ
ደግሞ ሁልጊዜ ራስህን ከፍ አድርገህ ታያለህ!” አለችው። ናትናኤልም፣
“አይ!... ማየት ሳይሆን እንቁላል የማይጥል ዶሮ ያለ ይመስል ገርሞኝ
እኮ ነው!” አለ። ኤደንም “ይኼውልህ መልሱ ዶሮ እንቁላል ሊጥልም፣
ላይጥልም ይችላል ነው” አለችው። ዘቢባም “ተመልከት ሁልጊዜ አውቃለሁ
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን ታሪኩን መሠረት በማድረግ በጽሑፍ መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
በምሳሌው መሠረት ጥያቄና መልስ ያለው ምልልሳዊ ጽሑፍ አዘጋጁ።
ናትናኤል፡- “አመሰግናለሁ።”
ቅድመማዳመጥ
የሚከተሉትን ቃላት ፍቺ ተናገሩ።
ቃላት
አቀላጥፎ ማንበብ
“ይቅርታ ጠይቂ!” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
7.1.4 መጻፍ
ምግባር
ሥነ
7.1.5 ክለሳ
ሀ. አ-ድ-ር-ገ-ሀ-ል ሐ. ተ-መ-ል-ከ-ት
ለ. መ-ቀ-በ-ል-ን መ. አ-ው-ቃ-ለ-ሁ
ሀ. ሳቀ ሐ. መጠየቅ
ለ. ረፍት መ. ይቅርታ
ጥሩ መጥፎ
ሥነምግባር ሥነምግባር
“የመልካም ሥነምግባር
7.2.1 ማዳመጥ
መገለጫዎች”
ቅድመማዳመጥ
ወላጆቻችሁን ወይም ታላላቆቻችሁን ለማስደሰት ምን ታደርጋላችሁ?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. ታ-ማ-ኝ-ነ-ት ሐ. ኃ-ላ-ፊ-ነ-ት
ለ. ሀ-ቀ-ኝ-ነ-ት መ. መ-ከ-ባ-በ-ር
ሀ. ኃላፊ ለ. ወጣት ሐ. ልጅ መ. ሰው
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
ታላላቆቻችሁን አክብሩ
አንድ ቀን አንድ አዛውንት ብዙ ዕቃ በትከሻቸው ተሸክመው ይሄዳሉ።
ከኋላቸው ነጂምና ሐና ከትምህርትቤት ወደቤታቸው ሲመለሱ አዛውንቱን
ከሩቅ አዩዋቸው። አዛውንቱ ትንሽ ሄደው ይቀመጣሉ፤ አሁንም ትንሽ
ሄደው ይቀመጣሉ። ሐናም “ነጂም አባባን አየሃቸው?” “ውይ! ሐና እኔም
ላሳይሽ ስል ነው የቀደምሽኝ። ሮጠን እንድረስባቸው?” አለ ነጂም። ሐናም
“አዎ! የአማርኛ መምህራችን ታላላቆቻችሁን አክብሩ፣ ከራሳችሁ ይልቅ
ለሌላ ሰው ቅድሚያ ስጡ አላሉንም?” አለችው። ነጂምም “ልክ ብለሻል
በይ ቶሎ እንድረስባቸውና ሸክማቸውን ተቀብለን እንሸኛቸው” አላትና
እየተሯሯጡ ሄዱ።
ቅድመንባብ
ሥዕሉን አስተውሉና ስለታሪኩ ገምቱ?
ኃላፊነትን መቀበል
ወይኒቱና ከማል የኹለተኛ ክፍል ተማሪዎች
ናቸው። ዛሬ በትምህርት ቤታቸው የፅዳት ዘመቻ
ይካሄዳል። መምህራቸው የክፍሉን ተማሪዎች
በስምንት ቡድን መደቧቸው። ወይኒቱና ከማልም
የየራሳቸውን የስራ ድርሻ ተቀበሉ። የእነወይኒቱ
የሥራ ድርሻ የመማሪያ ከፍሎችን አካባቢ
ማፅዳት ነበር። እነከማል ደግሞ የቢሮዎችንና
የሰንደቅዓላማ አካባቢዎችን ማፅዳት ነበር። ድንገት ከማል “መምህር” አለ።
“አቤት! ከማል ችግር አለ?” አሉት መምህሯ። “ለእኛ የተሰጠን ሥራ
ከእነወይኒቱ ይበልጣል” በማለት አጉረመረመ። መምህሯም “ሁላችሁም
የምታፀዱት የትምህርትቤታችሁን ግቢ ነው አሉት። ወይኒቱም “ከማል እኛ
ቶሎ ከጨረስን እናግዛችኋለን” አለችው።
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
“የመልካም ሥነምግባር
7.2.3 ማዳመጥ
መገለጫዎች”
ቅድመማዳመጥ
ለቃላቱ ተመሳሳይ ፍቺ ጻፉ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. እንሸኝላቸው
ለ. እንድረስባቸው
ሐ. እንቀበላቸው
መ. እናግዛቸው
“ሀ” “ለ”
1. ማክበር ሀ. መረገም
2. መሸከም ለ. መቀበል
3. መቀመጥ ሐ. መናቅ
4. መመረቅ መ. ማውረድ
ሠ. መቆም
አቀላጥፎ ማንበብ
“ታላላቆቻችሁን አክብሩ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
7.2.4 መጻፍ
ለ. የምታፀዱት መ. የትምህርትቤታችሁን
ማክበር
ለ. አባባን አገዝኳቸው ሮጬ
7.2.5 ክለሳ
ለ. የትምህርት - ቤት
ሀ. አፀዱ ሐ. ጠረጉ
ለ. አቃጠሉ መ. ሰበሰቡ
ቅድመማዳመጥ
ሥዕሉን አስተውሉና ስለታሪኩ ገምቱ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
1. ቃላቱን ድምፅ በማሰማት አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
ሀ. አይቻታለሁ ሐ. ሊተናኮሏት
ለ. እንቁራሪቷ መ. ማሳደዳችንን
“ሀ” “ለ”
1. መመለስ ሀ. መርሳት
2. ማሳደድ ለ. ደግነት
3. ክፋት ሐ. መሄድ
4. ማግኘት መ. መንከባከብ
5. ማለፍ ሠ. ማጣት
ረ. መውደቅ
ውሸታሙ እረኛ
በጫካ አጠገብ የሚኖር አርሶአደር ነበር። የሚያረባቸውን በጎች ቀበሮዎች
እየበሉበት ተቸገረ። በጎችን የሚጠብቅ እረኛ ቀጠረ። እረኛውንም መከረው።
“በጎችን ቀበሮ ሊበላ ሲመጣብህ ጩህ” ጩኸትህን ስንሰማ ተሯሩጠን
እንመጣለን” አለው።
ቅድመንባብ
እስከአሁን ካነበባችኋቸው መጻሕፍት የምትወዷቸውን ተናገሩ?
መጽሐፌ መካሪዬ
ያቺ መጸሐፌ/ የምወዳት፡
ብዙ ምክሮች/ በውስጧ አሏት፣
የማልሰለቻት/ ሁሌ አዲስ ናት።
ስለርህራሄ/ ትነግረኛለች፣
ስለዕውቀትም/ ታወራኛለች።
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በግጥሙ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
በምሳሌው መሠረት በግጥሙ ውስጥ የተገለፁትን ጠቃሚ ምክሮች ጻፉ።
ምሳሌ፡- ትዕግስት
ቅድመማዳመጥ
ለቃላቱ ተመሳሳይ ፍቺ ጻፉ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. እየወረወሩባት ሐ. ሩህሩህነት
ለ. ሊተናኮሏት መ. ማሳደዳችንን
ሀ. እንቁራሪት ሐ. እንዳትረግጣትም
ለ. ተመለከትካት
አቀላጥፎ ማንበብ
“ውሸታሙ እረኛ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
ሀ. ያቺ መጽሐፌ ሐ. ብዙ ምክሮች
ሀ. ሥነ-አዕምሮ ሐ. ሥነ-ሕይወት
ለ. ሥነ-ምግባር መ. ሥነ-ጽሑፍ
“ሀ” “ለ”
1. መታነፅ ሀ. ማውሳት
2. ውሸት ለ. ማፍቀር
3. ትዕግስተኛ ሐ. መገንባት
4. መልካም ምግባር መ. ሀሰት
5. ሩህሩህነት ሠ. ችኩል ያልሆነ
6. መውደድ ረ. አዛኝነት
ሰ. ጥሩ ባህርይ
ለ. አንድም ሰው ብቅ አላለም።
ቅድመማዳመጥ
ስለምታውቋቸው የምግብ ዓይነቶችና አዘገጃጀት ለክፍል ጓደኞቻችሁ ተናገሩ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. ይ-ለ-ቀ-ማ-ል ሐ. ይ-ከ-ካ-ል
ለ. ይ-ፈ-ጫ-ል መ. ይ-ታ-ጠ-ባ-ል
ምሳሌ፡- ኮረሪማ
የምግብ አቀራረብ
ቀኑ እሁድ ነበር። ወይዘሮ የዛብነሽ ምሳ ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ ይላሉ።
ሥራቸውን እንደጨረሱ ያዘጋጇቸውን ምግቦች መደርደር ጀመሩ። በአንድ
በኩል ዳቦ፣ እንጀራ፣ ሥጋ ወጥ፣ ጥብስ፣ ምንቸት አብሽ ደረደሩ። በሌላ በኩል
የወተት ተዋፅኦዎችን (እርጎና አይብ) አቀረቡ። ከአትክልትና ፍራፍሬዎች
ደግሞ አበሻ ጎመን፣ ጥቅል ጎመን፣ ቀይሥርና ካሮትን በቅደምተከተል
አስቀመጡ። ከዚህም በተጨማሪ ሙዝና ብርቱካን በአንድ ጎን ደረደሩ፡
በሌላ በኩል ደግሞ ሽሮወጥ፣ ምሥርወጥና ክክወጥ በጎድጓዳ ሳህን አቀረቡና
ለአፍታ ያህል ቃኘት በማድረግ ሳቅ አሉ።
ቅድመንባብ
ሰላጣ ምን ዓይነት ምግብ ይመስላችኋል?
የሰላጣ አዘገጃጀት
ሰላጣ የአትክልት ዓይነት ነው። በጥሬ ከሚበሉ የቅጠላቅጠል ዓይነቶች
ይመደባል። ሰላጣን በምግብነት ለማዘጋጀት የሚያስፈልጉ ግብኣቶች አሉ፤
እነሱም፡- ሰላጣ፣ ሎሚ/አቼቶ፣ ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ቃሪያ፣ ጨውና
የአትክልት ዘይት ናቸው።
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
በሥዕሎቹ መጠሪያ ቃላት ዓረፍተነገሮች መሥርቱ።
ቅድመማዳመጥ
ለሚከተሉት ቃላት ፍቺ ስጡ።
ቃላት
ሀ. ጥ-ራ-ጥ-ሬ ሐ. ይ-ደ-ር-ቃ-ል
ለ. ይ-በ-ጠ-ራ-ል መ. ዝ-ን-ጅ-ብ-ል
ለምሳሌ፡- አተር
አቀላጥፎ ማንበብ
“የምግብ አቀራረብ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
8.1.4 መጻፍ
ሀ. ይቀነጣጠሳል ለ. ይሰነጣጠቃል
ሀ. የዶሮ ወጥ ለ. እንጀራ
8.1.5 ክለሳ
ምሳሌ፡-
እርጎ ፓፓያ
ቅድመማዳመጥ
የዶሮ ወጥ እንዴት እንደሚሠራ ታውቃላችሁ? እስኪ ተናገሩ?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. እ-ን-ዲ-ላ-ቀ-ቁ ሐ. ይ-ገ-ሸ-ራ-ል
ለ. ይ-ለ-በ-ለ-ባ-ል መ. ይ-በ-ለ-ታ-ል
ቅድመንባብ
ርዕሱን አንብባችሁ ስለታሪኩ ገምቱ።
“የፈሰሰ ዉኃ…”
የዶሮ ወጡና የበጉ ጥብስ ጣት ያስቆረጥማል። እንዲሁም አይብ፣ እርጎና
በቅቤ የራሰ ክትፎ ተደርድረዋል። ጠላውና ጠጁ በጠርሙስና በብርሌ
በጠረጴዛ ላይ ቀርበዋል። ወይዘሮ ዘርፌ እንግዶቻቸው ዘግይተውባቸው
ወጣ ገባ ይላሉ። ድንገት ከወደኋላቸው የኳኳታ ድምፅ ሰሙ።
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
መ. ከታሪኩ ምን ተረዳችሁ?
የቃላት አጠቃቀም
ሠንጠረዡን በደብተራችሁ አዘጋጁና አሟልታችሁ ጻፉ።
ምግቦች መጠጦች
ምሳሌ፡- የበግ ጥብስ ጠላ
ቅድመማዳመጥ
የቃላቱን ተመሳሳይ ፍቺ ተናገሩ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. ማ-ስ-ተ-ካ-ከ-ል ሐ. እ-ን-ዲ-ላ-ቀ-ቁ
ለ. ተ-ቀ-ቅ-ለ-ው መ. በ-መ-ጀ-መ-ሪ-ያ
አቀላጥፎ ማንበብ
“የምግብ ዝግጅት ውድድር” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
8.2.4 መጻፍ
ሀ. ተደርድረዋል ሐ. እንግዶቻቸው
ለ. ተንቆርቁሯል መ. ይበረብራል
ምሳሌ፡- ድስት
8.2.5 ክለሳ
ቅድመማዳመጥ
ምግብ ለሰዎች ምን ጥቅም ይሰጣል?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. ሰ-ው-ነ-ታ-ች-ን ሐ. እ-ና-ድ-ጋ-ለ-ን
ለ. ተ-መ-ጣ-ጣ-ኝ መ. እ-ን-ጫ-ወ-ታ-ለ-ን
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
አሸናፊ ማነው?
ላም፣ በግ፣ ፍየልና ጎመን ለክርክር ከበሬ ዘንድ ቀረቡ። ላም “የሰው ልጆች
ሥጋዬን፣ እርጎዬንና ቅቤዬን ይመገባሉ። ወተቴን፣ አሬራዬንና አጓቴንም
ይጠጣሉ” አለች። በግ “እኔም ለሰው ልጅ ብዙ ጥቅም እሰጣለሁ፤ ክርክሩ
ስለምግብ ስለሆነ ሥጋዬ ለጥብስ፣ ለቅቅል፣ ለምንቸት አብሽ፤ ለአሮስቶና
ለመሳሰሉት ያገለግላል” አለች።
ቅድመንባብ
ከርዕሱ ምን ተረዳችሁ?
ምግቦች በበዓል ቀን
የተለያዩ እምነቶች ያሏቸው ሰዎች በበዓላት ወቅት የተለያዩ ምግቦችን
ያዘጋጃሉ። ለምሳሌ፣ በእስልምና እምነት በኢድአልፈጥር ዕለት ለቁርስ
በአብዛኛው ገንፎ ይገነፋል። ገንፎው ከገብስ፣ ከስንዴ ከመሳሰሉት ሊዘጋጅ
ይችላል። ለምሳ ደግሞ ሥጋወጥ፣ ጥብስ፣ ክትፎና የመሳሰሉት ከለስላሳ
መጠጦች ጋር ተዘጋጅተው ይቀርባሉ።
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
“ሀ” “ለ”
1. ገንፎ ሀ. ይጠመቃል
2. ቂጣ ለ. ይጠበሳል
3. ጥብስ ሐ. ይጣላል
4. ወጥ መ. ይጋገራል
5. ጠላ ሠ. ይገነፋል
ረ. ይሠራል
ቅድመማዳመጥ
ለቃላቱ ተመሳሳይ ፍቺ ስጡ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
አቀላጥፎ ማንበብ
“አሸናፊ ማነው?” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
ሀ. ሚ-ሻ-ሚ-ሾ ሐ. ፀ-ሎ-ተ-ሀ-ሙ-ስ
ለ. ኢ-ድ-አ-ል-ፈ-ጥ-ር መ. በ-አ-ላ-ቸ-ው
ሀ. እንጀራ ለ. ጠላ ሐ. ዳቦ መ. ጠጅ
ምግብ
ዳቦ ሥጋ ጎመን
ቅድመማዳመጥ
ሀ. ሥዕሎቹን አስተውሉና ስለታሪኩ ገምቱ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. ሬ-ዲ-ዮ ሐ. አ-ድ-ማ-ጮ-ች
ለ. ቴ-ሌ-ቪ-ዥ-ን መ. ታ-ዳ-ሚ-ዎ-ች
የወንድሜ ስልክ
ወንድሜ የአስራ ኹለተኛን ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈትኖ ወደዩኒቨርሲቲ
የሚያስገባ ውጤት አመጣ። ሁላችንም በጣም ተደሰትን። ወንድሜም ጎንደር
ዩኒቨርሲቲ ተመደበ። ለወትሮው ተለይቶን ስለማያውቅ እጅግ ግራ ተጋባን።
ምንም እንኳ የምንኖረው በገጠር ቢሆንም ስለስልክ ምንነት በመጠኑም ቢሆን
እናውቃለን። ስለዚህ ኹለት ስልኮች ገዛን። የወንድሜ ስልክ በጣም ያምራል።
በውስጡ ብዙ ነገሮችን ይዟል። ፎቶ ያነሳል፣ ከበይነመረብ/ኢንተርኔት የተለያዩ
መረጃዎችን ይቀበላል፣ ይልካል። ወንድሜ ሙዚቃዎችን፣ ፊልሞችን በስልኩ
ጭኖ ያዳምጣል፣ ይመለከታል። የወንድሜ ወደዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ቀን
ሲደርስ ሁላችንም በስልኩ ፎቶ ተነሳን።
ቅድመንባብ
ከሥዕሉ ምን ትረዳላችሁ?
“የመጀመሪያዋ ቀን”
አንዲት የገጠር ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአጎቷ ጋር
ወደከተማ ሄደች። ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከተማ ደረሱ።
ከተማው በመብራቶች አሸብርቋል። ልጅቷ እጇን
አፏ ላይ አድርጋ በዝምታ ታያለች። አጎቷም ግራ
እንደተጋባች አውቆ“ ከተማችንን አየሽው?” አላት።
“አዎ! ጋሼ! ምኑ ነው እንዲህ የሚንቀለቀለው?” አለችው። “ይሄውልሽ ይህ
በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠራ መብራት ነው። በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠሩ
ብዙ ዓይነት መሣሪያዎች አሉ።
ለምሳሌ ስልክ፣ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣ የዉኃ
ማጣሪያ ማሽን፣ የምግብ ማብሰያ ማሽን፣ የምግብ ማቀዝቀዣ ማሽን፣ የሻሂ
120 አማርኛ 2ኛ ክፍል ~ የተማሪ መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ዲጂታል መሣሪያዎች )!
ማፍያ ማሽን፣ ካሜራና ሌሎችም የሚሠሩት በኤሌክትሪክ ኃይል ነው”
አላት። ልጅቷም “አሁን የጠራሃቸው ዕቃዎች ሁሉ በቤትህ ውስጥ አሉ?”
አለችው። “አዎ! ከቤት ስንደርስ ሁሉንም አሳይሻለሁ” አላት።
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
ሀ. ልጅቷ እጇን አፏ ላይ አድርጋ በዝምታ የምታየው ለምን ይመስላችኋል?
ለ. ኤሌክትሪክ ባይኖር በኑሯችን ላይ ምን ችግር የሚፈጠር ይመስላችኋል?
የቃላት አጠቃቀም 1
ቅድመማዳመጥ
የሚከተሉትን ቃላት ፍቺ ተናገሩ።
ሀ. ድራማ ለ. ፊልም ሐ. ታዳሚ
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. የተሸላ ሐሳብ የሚቀርብበት ሬድዮ ወይስ ቴሌቪዥን ይመስላችኋል?
ለ. በመጨረሻስ ልጅቱ ምን የምትል ይመስላችኋል? ለምን?
ሐ. ከቴሌቪዥንና ከሬዲዮ በቀላሉ ከቦታ ወደቦታ አንቀሳቅሶ ለመጠቀም
የሚመቸው የትኛው ነው? ለምን?
አቀላጥፎ ማንበብ
“የወንድሜ ስልክ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
9.1.4 መጻፍ
1. ሀ. ሬዲዮ
2. ለ. ቴሌቪዥን
3. ሐ. ስልክ
4. መ. ባትሪ
5. ሠ. ካሜራ
ለ. ስልክ
9.1.5 ክለሳ
ኤልሃና፤ ________
ከድር፤ ________
ኤልሃና፤ ________
ቅድመማዳመጥ
ሥዕሉን አስተውሉና ስለታሪኩ ገምቱ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን ባዳመጣችሁት ታሪክ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. ኮ-ም-ፒ-ዩ-ተ-ር
ለ. መ-ጠ-ቆ-ሚ-ያ
ሐ. የ-ኮ-ም-ፒ-ዩ-ተ-ር-ሰ-ሌ-ዳ
መ. መ-ተ-ግ-በ-ሪ-ያ
124 አማርኛ 2ኛ ክፍል ~ የተማሪ መጽሐፍ ~ ምዕራፍ 9 ዲጂታል መሣሪያዎች )!4
2. ቃላቱን ድምፅ በማሰማት አንብቡና ጻፉ።
ለ. መጠቆሚያ መ. መተግበሪያ
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
ቅድመንባብ
ሀ. “ሲሮጡ የታጠቁት ሲሮጡ ይፈታል” ከሚለው ሐሳብ ምን ትረዳላችሁ?
“ሲሮጡ የታጠቁት...”
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
የሥዕሎቹን መጠሪያ ቃላትና የአገልግሎት ልዩነታቸውን ጻፉ።
12
11 1
10 2
9 3
8 4
7 5
6
ቅድመማዳመጥ
ለቃላቱ ተመሳሳይ ፍቺ ስጡ።
ሀ. ጠርዝ ለ. ሌባ ጣት ሐ. መጠቆሚያ
ቃላት
አቀላጥፎ ማንበብ
“ዓይነሥውሩ ተማሪና ስልኩ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
9.2.4 መጻፍ
ሀ. ን-ብ-ረ-ቶ-ች ሐ. የ-እ-ጅ-ሰ-ዓ-ት
ለ. የ-ሒ-ሳ-ብ-ማ-ሽ-ን መ. የ-ስ-ል-ክ-መ-ጠ-ገ-ኛ
ሀ. በካሴት ለ. በካሜራ
9.2.5 ክለሳ
ምሳሌ፡- ስልክ
ቅድመማዳመጥ
መገናኛ ብዙኃን ምን ማለት ነው?
ቃላት
ሀ. መ-ል-ዕ-ክ-ት ሐ. ማ-ስ-ተ-ላ-ለ-ፊ-ያ
ለ. ማ-ሰ-ራ-ጫ መ. ባ-ለ-ሙ-ያ
ሀ. መልእክት ሐ. ርዕስ
ለ. ድርጅት መ. መገናኛ
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ምልልሳዊ ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
የተሳሳተ የስልክ ጥሪ
ደዋይ “ሄሎ!”
ቅድመንባብ
ርዕሱን አስተውሉና ታሪኩ ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ።
“የማስጠንቀቂያ ደወል”
በቃሉ የድራማና የሥነፅሁፍ አስተባባሪ
ነው። በጧቱ ተነስቶ መቅረፀድምፁን
በሰንደቅዓላማ ማክበሪያ ቦታ አዘጋጀው።
የመዝናኛ ሙዚቃዎችን የያዘውን ካሴት
በመቅረፀ ድምፁ አስገባና ከፈተው።
ተማሪዎች በሙዚቃው እየተነቃቁ
ወደሰንደቅዓላማው ቦታ ተመሙ።
የቃላት አጠቃቀም
በትምህርትቤታችሁ በሰልፍ ላይ በድምፅ ማጉያ የሚተላለፉ ትዕዛዛዊ
መልእክቶችን በቡድን ሆናችሁ በዝርዝር ጻፉ።
ቅድመማዳመጥ
ለቃላቱ ተመሳሳይ ፍቺ ስጡ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ዓይነት
ምሳሌ፡-
የመገናኛ ብዙኃን
አቀላጥፎ ማንበብ
“የተሳሳተ የሰልክ ጥሪ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
9.3.4 መጻፍ
ሀ. ሥ-ነ-ጽ-ሑ-ፍ ሐ. ድ-ም-ፅ-ማ-ጉ-ያ
ለ. መ-ዝ-ና-ኛ
ጽሑፍ
ሥነ
9.3.5 ክለሳ
ሀ. ዘጋ ሐ. ደወለ
ለ. ደነገጠ መ. ተቀበለ
ምሳሌ፡-
ቅድመማዳመጥ
ሀ. ጉልበት ምንድን ነው? ብልሃትስ?
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. ጉ-ል-በ-ት ሐ. መ-ሮ-ጫ-ው
ለ. ብ-ል-ሃ-ት መ. ው-ድ-ድ-ር
ሀ. ቀረቡ ለ. ዞረ ሐ. ሥር
የሌሊት ወፍ
በድሮ ጊዜ ቀን ቀን የሌሊት ወፍ የጓደኞቿን ምግብ እየተበደረች ትበላ ነበር።
ከጊዜ በኋላ ብድሯን መክፈል ሲያቅታት ከሌሎች ወፎች ለመሰወር ወሰነች።
ከጉጉት ጋርም በሌሊት መኖር ጀመረች። የድሮ ሰዎች “በዚህ የተነሳ ሌሊት
እንጂ ቀን አትበርም” ይላሉ። ያም ሆነ ይህ የሌሊት ወፍ ከሌሎች ወፎች
በእጅጉ ትለያለች። እንደሰው አጥቢ ናት። ቀን ቀን በተቦረቦረ ዛፍ ውስጥ፣
ጨለምለም ባለ ቦታ ወይም በዋሻ ውስጥ ታሳልፋለች። ስትተኛም ክንፏን
በማጠፍ ራሷን ዘቅዝቃ ነው። ልጆቿንም በድምጻቸው ትለያለች። የሌሊት
ወፍ ለስልሳ ቀናት ያህል ሳታቋርጥ ልጆቿን ትመግባለች። በአማካይ
ለዐምስት ዓመታት በሕይወት ትኖራለች።
ቅድመንባብ
ሥዕሉን አስተውሉና ታሪኩ ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ።
ነብርና ድኩላ
ነብርና ድኩላ በአንድ ላይ ተስማምተው ለመኖር
ተማማሉ። በአንድ ላይ ሲኖሩ የድኩላ አካሉ
እየሞላ፣ ሰውነቱ እየጨመረ፣ እያብረቀረቀ ይታይ
ጀመር። ነብርም ይህንን አይቶ መሀላውን ሊያፈርስ
ከጀለና ተቅበጠበጠ። አንድ ቀን ለሽርሽር ራቅ ወዳለ ቦታ ሄዱ። ነብርም
“ድኩላን መሃላ ቢፈርስ ምን ይሆናል?” ብሎ ጠየቀው። ድኩላም “በልጅ
ይደርሳል” አለው። ነብርም “አሃ! እንደዚህ ከሆነማ! ብሎ በድኩላው አካል
ላይ ተከመረበት። ድኩላም ባልሞት ባይ ተጋዳይነት ሲፈራገጥ ቀንዱ
በነብሩ ሆድ ላይ ተሰካ። ነብርም እያቃሰተ ‘መሃላ የሚደርስ በልጅ ነው’
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
“ነብርና ድኩላ” በሚለው ታሪክ ላይ ያለውን ሥዕል በማስተዋል በነብርና
በድኩላ መካከል ያሉትን ልዩነቶች ግለጹ።
ምሳሌ፡-
ነብር ድኩላ
ቅድመማዳመጥ
ለቃላቱ ተመሳሳይ ፍቺ ስጡ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
ቃላት
አቀላጥፎ ማንበብ
“የሌሊት ወፍ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
10.1.4 መጻፍ
ዓሳ እንቁራሪት ጉጉት
የሌሊት ወፍ ዓሳ
ምሳሌ፡- ጉጉት
የምትኖረው የት ነው?
ቅድመማዳመጥ
ስለብርቅዬ የዱር እንስሳት የምታውቁትን ተናገሩ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. እንደዋልያ ሐ. እንደዝሆን
ለ. እንደአይጥ መ. እንደከበሮ
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
ዶልፊንና ዐዞ
በዉኃ ውስጥ ከሚኖሩ እንስሳት መካከል
ዶልፊንና ዐዞ ይጠቀሳሉ። ሁለቱም የተለያየ
አፈጣጠርና ባህርይ አላቸው። ዶልፊኖች
ልክ እንደሰው፣ ሰዎችን የሚንከባከቡ፣
የሚወዱና የማይተናኮሉ ናቸው። ዐዞዎች ግን ሰዎችን በሹል ጥርሳቸው
የሚቀረጥፉ አደገኛ ፍጡሮች ናቸው። ዶልፊኖች እንደሌሎች አጥቢዎች
መሰላቸውን በመውለድ ይራባሉ። ዐዞዎች ደግሞ እንቁላል በማስፈልፈል
ይራባሉ። ዶልፊን በአንድ ጊዜ አንድ በመውለድና በማጥባት ታሳድጋለች።
ዐዞ ግን እስከአስራ ዐምስት እንቁላሎች በዉኃ ዳር በሚገኝ አሸዋ ውስጥ
ትጥልና ትቀብራለች። ጊዜው ሲደርስ አሸዋውን ትምሳለች። የሚፈለፈሉት
ዐዞዎች እንቁላሎቻቸውን ከውስጥ ሆነው በመስበር ይፈለፈላሉ። ከዚያም
እየተሯሯጡ ወደወንዙ ወይም ወደሐይቁ ይገባሉ።
ቅድመንባብ
ጉንዳንና ዋኔ ምን ዓይነት እንስሳት ይመስሏችኋል?
ጉንዳንና ዋኔ
ከዕለታት በአንድ ቀን ጉንዳን ለመሻገር ወደአንድ ጅረት አመራ። ወደወንዙ
ሲገባ የወንዙ ማዕበል ክፉኛ አንገላታው። ዋኔ በአፏ የቅጠል ዝንጣፊ ይዛ
በጅረቱ አናት ላይ ትበራለች። ዋኔዋም ጉንዳኑ ከወዲያ ወዲህ ሲንገላታ
አየችው። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ማዕበሉ እንደሚያሰጥመው ተረዳች። ዋኔዋ
በጉንዳኑ ትይዩ ዝቅ ብላ በመብረር የያዘችውን ዝንጣፊ ቅጠል ቁልቁል
ወረወረችለት። ጉንዳኑም በዝንጣፊው ቅጠል ላይ በመሆን ራሱን አዳነ። በሌላ
ቀን አንድ ልጅ ዋኔዋን በወጥመድ ያዛት። ዋኔዋም ለማምለጥ ስትፈራገጥ
ጉንዳኑ አያት። ቀስ ብሎ ተጠጋና የልጁን እግር ክፉኛ ነከሰው። ልጁ
ደንግጦ የወጥመዱን ገመድ ለቀቀው።
ድኅረንባብ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በጽሑፍ መልሱ።
የቃላት አጠቃቀም
በሚከተሉት ቃላት ዓረፍተነገር መሥርቱ።
ቅድመማዳመጥ
ዋልያና ቀይ ቀበሮ ምን ዓይነት እንስሳት ይመስሏችኋል?
ድኅረማዳመጥ
ሀ. በምሳሌው መሠረት ጻፉ።
ቃላት
ሀ. ብሔራዊ ሐ. ሥርዓት
ለ. ብርቅዬ መ. አመጋገብ
ሀ. ዋልያዎች ሐ. እንስሳዎች
ለ. ቡችላዎች መ. አጥቢዎች
አቀላጥፎ ማንበብ
“ዶልፊንና ዐዞ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
ሀ. ቁ-ል-ቁ-ል ሐ. ሲ-ን-ገ-ላ-ታ
ለ. ዝ-ን-ጣ-ፊ መ. ስ-ት-ፈ-ራ-ገ-ጥ
ሀ. አየችው ሐ. ነከሰው
ለ. ያዘችው መ. ለቀቀው
ሀ. ቁልቁል ለ. መንገላታት
ሐ. መወርወር መ. መንከስ
አንበሳ ቀጭኔ
ስጋ ዕፅዋት
የሚመገቡ የሚመገቡ
ጦጣ ተጠራች።
ቅድመማዳመጥ
ሥዕሉን አስተውሉና ስለታሪኩ ገምቱ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎቹን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ሀ. ኢ-ት-ዮ-ጵ-ያ ሐ. አ-ፍ-ሪ-ካ
ለ. ዓ-ለ-ማ-ች-ን መ. ኩ-ን-ቢ-ያ-ቸ-ው
“ሀ” “ለ”
1. ዝሆን ሀ. አፍንጫ
2. ቀጭኔ ለ. ስንጥብ
3. ዓሣ ሐ. ኩምቢ
አቀላጥፎ ማንበብ
የሚከተለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
ቀጭኔ
ቀጭኔዎች በአፍሪካ አህጉር በብዛት የሚገኙ የዱር
እንስሳት ናቸው። እንደዝሆኖች ጡት አጥቢዎች ናቸው።
ሽሆናቸው ደግሞ እነደቀንድ ከብቶች መሀሉ ስንጥቅ
ነው። በምድር ላይ ከሚገኙ እንስሳት በርዝመታቸው
አንደኛ ናቸው። ወንዱ ቀጭኔ ከሴቷ ትንሽ ይረዝማል።
ቀጭኔዎች አንገታቸው እጅግ ረዥም ከመሆኑ የተነሳ
ከረዣዥም ዛፎች ቅጠላቅጠልንና ፍራፍሬን በመቀንጠስ
ይመገባሉ። የቀጭኔዎች ምላስም በጣም ረዥም ስለሆነ ጆሯቸውን ለማፅዳት
ያስችላቸዋል።
ቅድመንባብ
ሠንጠረዡን በደብተራችሁ አዘጋጁና ስለጥርኝ የምታውቁትንና ማወቅ
የምትፈልጉትን በተመለከተ አሟልታችሁ ጻፉ።
ጥርኝ
ጥርኞች በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ አጥቢ እንስሳት ናቸው። ጥርኞች ሥጋ
በል ከሆኑ እንስሳት ይመደባሉ። በአማካይ ከአንድ እስከአራት ቡችሎችን
በጉድጓድ ውስጥ ይወልዳሉ። የጥርኝ ቡችሎች በተወለዱ በዐምስት ቀናቸው
መራመድ ይችላሉ። ጥርኞች ከሰውነታቸው የሚያመነጩት ዝባድ የሚባል
ፈሳሽ አላቸው። ቡችሎቹ ከተወለዱ ከዐምስት ወራት ጀምሮ ዝባድ ያመነጫሉ።
ዝባዱ ደስ የሚል ጠረን አለው። ዝባዱን የሚይዙት ከመፀዳጃቸው ጥግ ባለ
ከረጢት መሰል አካላቸው ውስጥ ነው። ዝባዱ በመጀመሪያ ቢጫ የመሰለ
ቅባት ሲሆን እየቆየ ሲሄድ ይጠጥርና ጥቁር ቡናማ መልክ ይኖረዋል።
ሰዎች የጥርኝን ዝባድ ለማግኘት ጥርኞችን በየቤታቸው ያረቧቸዋል።
ዝባዱም ከሌሎች ንጥረ ነገሮች ጋር ተቀምሞ ሽቶ ይሆናል።
ምን ተማርኩ?
ጥርኝ የምታመነጨው ፈሳሽ ዝባድ ይባላል።
የቃላት አጠቃቀም
ሥዕሎቹን በማስተዋል ልዩነታቸውንና ተመሳስሏቸውን ግለጹ።
ቅድመማዳመጥ
ለቃላቱ ፍቺ ስጡ።
ድኅረማዳመጥ
ጥያቄዎችን በታሪኩ መሠረት በቃል መልሱ።
ቃላት
ሀ. በ-ር-ዝ-መ-ታ-ቸ-ው ሐ. ጆ-ሯ-ቸ-ው-ን
ለ. አ-ን-ገ-ታ-ቸ-ው መ. ያ-ስ-ች-ላ-ቸ-ዋ-ል
አቀላጥፎ ማንበብ
“ቀጭኔ” የሚለውን ታሪክ አቀላጥፋችሁ አንብቡ።
10.3.4 መጻፍ
ሀ. ጥርኝ ለ. ቅባት ሐ. ሽቶ
ሀ. ጥርኞች ሐ. ከረጢቶች
ለ. ቡችሎች መ. እንስሶች
“ሀ” “ለ”
1. ሴት ሀ. ድፍን
2. ትልቅ ለ. የቆሸሸ
3. ረዥም ሐ. ወንድ
4. የፀዳ መ. ትንሽ
5. ስንጥቅ ሠ. አጭር
ረ. ከባድ
የዱር
ዝሆን ቀጭኔ
እንስሳት
በኩምቢው በአፍንጫዋ
ናቸው።
ይተነፍሳል። ትተነፍሳለች።
ምንነት
አፈጣጠር
ጥቅም
ትምህርት ሚኒስቴር። (2006)። አማርኛ እንደአፍ መፍቻ ቋንቋ የተማሪ መጽሐፍ። አዲስ አበባ።
ትምህርት ሚኒስቴር። (2006)። አማርኛ እንደአፍ መፍቻ ቋንቋ የመምህር መጽሐፍ። አዲስ አበባ።
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ። (1996)። የአማርኛ 2ኛ ክፍል መማሪያ
መጽሐፍ። ባሕር ዳር።
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ። (1996)። የአማርኛ 3ኛ ክፍል መማሪያ
መጽሐፍ። ባሕር ዳር።
ዘሪሁን አስፋው። (1992)። የሥነ ጽሑፍ መሠረታውያን። አዲስ አበባ። ንግድ ማተሚያ ድርጅት